zethiopia, ethiopian american community news no.92 … 92.pdf · zethiopia, ethiopian american...

16
Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com [email protected] ዘኢ ዮጵያ 712-432-7777 እኛ ወደብ መች ቸገረን... ወደብ ልማት ያመጣል ብለው የሚያስቡ ሰዎች ስለ ኢኮኖሚ ልማት ምንም የማይገባቸው ሰዎች ናቸው ኤርትራና ሶማልያን እይዋቸው! Mengehsa indicted for killing detective አትላንታ- አማኑኤል መንገሻ የካውንቲውን ፖሊስ ተኩሶ ገደለ ሳንፍራንሲስኮ - ሰለሞን ዓለሙ የሰው መኪና ነጥቆ በረረ- ከኋላ የ4 ወር አራስ ልጅ ስለ ምርጫው- “ይኼ እንደ ሰሜን ኮሪያ ባሉ አገሮች የሚከሰት ነገር ነው” ስተለቃዋሚዎች ፓርቲዎች - “የተከፋፈሉ መሆናቸውንም ተመልክቻለሁ” ስለ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ - “በተገቢው ሁኔታ ስለመያዛቸው ለማረጋገጥ አልቻልንም” ስለ ግንቦት ሰባት- “እንግሊዝ ግንቦት ሰባትን በሽብርተኝነት አልፈረጀችም!” በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር አምባሳደር ግሬግ ዶሪ ምስክርነት አቶ አርከበ እቁባይ ገጽ 2 “በነገራችን ላይ የአርሴናል ፕሮፌሽናል ተጫዋች ሆኖ የተመዘገበው ጌዲዮን ዘላለም በመካከላችን ይገኛል” በማለት የስፖርት ፌዴሬሽኑ የረጅም ዘመን ቃል አቀባይ ሆነው የሚሠሩትና የዕለቱም አጋፋሪ ሆኖ የታዩት የዳላሱ ኮምዩኒቲ ሬድዮ አዘጋጅ አቶ ዘውገ ቃኘው ሲናገሩ ጌዲዮን ከወላጆቹና ከፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ጋር ታጅቦ ወደ መድረኩ አምርቷል። በፎቶ ግራፉ ላይ የሚታዩት የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳትን አቶ ጌታቸው ተስፋዬ ከመሃል ጌዲዮን እና በፌዴሬሽኑ የቀድሞ የህዝብ ግንኙነት አቶ ፋሲል ናቸው። የጌዲዮን አባት ከኋላ መኃል ላይ ይታያሉ። ለዘገባው ገጽ 6 (ፎቶ ኢትዮቱብ) በመክፈቻው ላይ የተገኘው ሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአየርላንድ ርዕሰ ከተማ ደብሊን በኩል ወደ አሜሪካ ሎሳንጀለስ የጀመረውን አዲስ በረራ ለማስመረቅ ጁን 27 ደብሊን አርፏል። የአውሮፕላኑ መንገደኞች የነበሩ 8 ኢትዮጵያውያን ፣ አውሮፕላኑ እንዳረፈ ወዲያውኑ ወደ ኢሚግሬሽን ክፍሉ አምርተው ጥገኝነት መጠየቃቸው ሲያነጋግር ሰንብቷል። ሁለት ህጻናትን ጨምሮ የፖለቲካ ጥገኝነት የጠየቁት 6 መንገደኞች በአውሮፕላን ማረፊያ ጣቢያው ሲደርሱ ምንም አይነት መታወቂያ ወይም የጉዞ ሰነዶችን አለመያዛቸውን አሳውቀዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቃል አቀባይ ግን፣ የአውሮፕላኑ ተሳፋሪዎች በሙሉ ከአዲስ አበባ ሲነሱ ህጋዊ ሰነዶችን ይዘው እንደነበር እንደሚያውቁና ስለ ፖለቲካ ጥገኝነት ጠያቂዎቹ የግል ጉዳይ ግን አስተያየት መስጠት አንፈልግም ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያም መንግሥት ለህትመት እስከገባንበት ሳምንቱ መጀመሪያ ድረስ በጉዳዩ ላይ ምንም መግለጫ ሳይሰጥ ቆይቷል። መንግሥት መንገደኞቹ ወደ አገር ተይዘው እንዲመለሱ እየተደራደረ መሆኑን የገመቱ ቢኖሩም የአየር ላንድ መንግሥት ምን እንዳደረገ ወይም ማድረግ እንዳሰበ በቅርብ ጊዜ ውስጥ አልተገለጸም። የከፋውም የደላውም፣ ፓይለቱም ፣መንገደኛውም በየብስም በውሃም እናም ደግሞ ዛሬም በአየርም አገር እየጣለ የሚወጣበት ምክንያት ለብዙዎች እንቆቅልሽ እየሆነ ነው። ስደተኞቹ የኢኮኖሚ እንጂ የፖለቲካ ችግር የለባቸውም ሲል የኖረው መንግሥት ኢኮኖሚው አድጓል እየተባለ ባለበትም ቁጥር ሰዎች አገር ጥለው መኮብለላቸው አስገራሚ ይመስላል። 8 የኢትዮጵያ አየር መንገድ መንገደኞች ጥገኝነት ጠየቁ መንግስት አይ.ኤስ.አይ.ኤስን ለመቃወም በጠራው ሰልፍ ሰበብ እስር ላይ ቆይተው እንዲፈቱ ተወስኖላቸው ከእስር ቤት ሲወጡ እንደገና በፖሊስ ተይዘው የታሰሩት ወንይሸት ሞላ፣ ኤርሚያስ ፀጋዬ፣ ዳንኤል ተስፋዬና ቤትሄልየም አካለወርቅ ላይ ፖሊስ አዲስ ክስ አቀረበ፡፡ እነ ወይንሸት ሰኔ 18/2007 ዓ.ም ቀደም ብለው ተከሰውበት በነበረው ተመሳሳይ ‹ወንጀል› ፖሊስ የምርመራ መዝገብ ይዞ ቀደም ብለው ውሳኔ ባገኙበት በተመሳሳይ ቄራ ፍርድ ቤት ቀርበው ዳኞቹ ‹‹እኛ ፈርደናል፤ እንዲለቀቁም ወስነናል፣ ከዚህ በኋላ ይህን ጉዳይ አናይም›› በሚል መዝገቡን እንደማያዩ ገልጸው መመለሳቸው ይታወቃል፡፡ ይሁንና ዛሬ ሰኔ 19/2007 ዓ.ም በቄራ መጀመሪያ ፍርድ ቤት ቀርበው ፖሊስ ‹‹ምስክሮችና የምስክሮቹ ጓደኞች ላይ ዛቻና ማስፈራሪያ አድርሰውብኛል›› ሲል ሌላ ክስ አቅርቧል፡፡ ፖሊስ እነ ወይንሸት ሰኔ 15/2007 ዓ.ም በቄራ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት ቀርበው እንዲፈቱ ከተወሰነላቸው በኋላ ፍርድ ቤቱ ግቢ ውስጥ የነበሩትን ምስክሮችና የምስክሮች Obama is Under fire for visiting Ethiopia page 11 Hammond: Andy Tsege detention ‘undermining UK-Ethiopia relations page 11 ሰማያዊዎችን ፍርድ ቤት ሲለቃቸዉ ፖሊስ ያዛቸዉ ጓደኞችን ‹‹ወያኔ ለዘላለም አይኖርም፣ እንገናኛለን፣ ቤታችሁን እናውቀዋለን፣ የወያኔ ተላላኪዎች›› በሚል ዛቻና ማስፈራሪያ አድርሰውብኛል ብሏል፡፡ ሆኖም እነ ወይንሸት በወቅቱ የመሰከሩባቸውን ሰዎች ፍርድ ቤቱ ግቢ ውስጥ እንዳላዩዋቸው፣ ዛቻና ማስፈራሪያም እንዳላደረሱባቸውና ክሱ ሆን ተብሎ እስር ላይ ለማቆየት የተደረገ ነው ብለዋል፡፡ እነ ወይንሸት በአዲሱ ክስም የዋስትና መብት የተከለከሉ ሲሆን በምስክሮችና የምስክሮች ጓደኞች ላይ ዛቻና ማስፈራሪያ አድርሰውብኛል ያለው ፖሊስ ምስክር ለማሰማት ለማክሰኞ ሰኔ 23/2007 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቶታል፡፡ (በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር) ተገድሏል የሰማያዊው ፓርቲ ዕጩ ሳሙኤል አወቀ Model’s split from husband finally made public page 13 Lemn Sissay announced as next University of Manchester Chancellor page 9 ገጽ 14 ገጽ 5 ባቡር በቻይንኛ ምንድነው? ገጽ 3 አየር መንገዱ ከ2 ነጥብ 6 ቢሊየን ዶላር በላይ ወጪ ስድስት ተጨማሪ 787 ድሪምላይነር አዘዘ ቦይንግም ተገላገለ ይድረስ ለውድ ፕሬዚደንት ዙማ፣ ገጽ 12 32ኛው የኢትዮጵያን ስፖርት በዓል በሜሪላንድ እየተካሄደ ነው ገጽ 4 ገጽ 2

Upload: nguyentuong

Post on 14-Feb-2018

310 views

Category:

Documents


44 download

TRANSCRIPT

Page 1: Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 … 92.pdf · Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, ... በቀድሞው

Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com

202 518 0245 P.o.box 2049,

Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com

[email protected]

ዘኢትዮጵያ

712-432-7777

እኛ ወደብ መች ቸገረን...ወደብ ልማት ያመጣል ብለው የሚያስቡ ሰዎች

ስለ ኢኮኖሚ ልማት ምንም የማይገባቸው ሰዎች ናቸው ኤርትራና ሶማልያን

እይዋቸው!

Mengehsa indicted for

killing detectiveአትላንታ- አማኑኤል መንገሻ የካውንቲውን ፖሊስ ተኩሶ ገደለ

ሳንፍራንሲስኮ - ሰለሞን ዓለሙ የሰው መኪና ነጥቆ በረረ- ከኋላ የ4 ወር አራስ ልጅ

ስለ ምርጫው- “ይኼ እንደ ሰሜን ኮሪያ ባሉ አገሮች የሚከሰት ነገር ነው”

ስተለቃዋሚዎች ፓርቲዎች - “የተከፋፈሉ መሆናቸውንም

ተመልክቻለሁ”

ስለ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ - “በተገቢው ሁኔታ ስለመያዛቸው

ለማረጋገጥ አልቻልንም”

ስለ ግንቦት ሰባት- “እንግሊዝ ግንቦት ሰባትን በሽብርተኝነት አልፈረጀችም!”

በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር አምባሳደር ግሬግ ዶሪ ምስክርነት

አቶ አርከበ እቁባይ ገጽ 2

“በነገራችን ላይ የአርሴናል ፕሮፌሽናል ተጫዋች ሆኖ የተመዘገበው ጌዲዮን ዘላለም በመካከላችን ይገኛል” በማለት የስፖርት ፌዴሬሽኑ የረጅም ዘመን ቃል አቀባይ ሆነው የሚሠሩትና የዕለቱም አጋፋሪ ሆኖ የታዩት የዳላሱ ኮምዩኒቲ ሬድዮ አዘጋጅ አቶ ዘውገ ቃኘው ሲናገሩ ጌዲዮን ከወላጆቹና ከፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ጋር ታጅቦ ወደ መድረኩ አምርቷል። በፎቶ ግራፉ ላይ የሚታዩት የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳትን አቶ ጌታቸው ተስፋዬ ከመሃል ጌዲዮን እና በፌዴሬሽኑ የቀድሞ የህዝብ ግንኙነት አቶ ፋሲል ናቸው። የጌዲዮን አባት ከኋላ መኃል ላይ ይታያሉ። ለዘገባው ገጽ 6 (ፎቶ ኢትዮቱብ)

32ኛ የኢትዮጵያውያን ስፖርት በዓል በሜሪላንድ እየተካሄደ ነው በመክፈቻው ላይ የተገኘው ሰው

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአየርላንድ ርዕሰ ከተማ ደብሊን በኩል ወደ አሜሪካ ሎሳንጀለስ የጀመረውን አዲስ በረራ ለማስመረቅ ጁን 27 ደብሊን አርፏል። የአውሮፕላኑ መንገደኞች የነበሩ 8 ኢትዮጵያውያን ፣ አውሮፕላኑ እንዳረፈ ወዲያውኑ ወደ ኢሚግሬሽን ክፍሉ አምርተው ጥገኝነት መጠየቃቸው ሲያነጋግር ሰንብቷል።

ሁለት ህጻናትን ጨምሮ የፖለቲካ ጥገኝነት የጠየቁት 6 መንገደኞች በአውሮፕላን ማረፊያ ጣቢያው ሲደርሱ ምንም አይነት መታወቂያ ወይም የጉዞ ሰነዶችን አለመያዛቸውን አሳውቀዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቃል አቀባይ ግን፣ የአውሮፕላኑ ተሳፋሪዎች በሙሉ ከአዲስ

አበባ ሲነሱ ህጋዊ ሰነዶችን ይዘው እንደነበር እንደሚያውቁና ስለ ፖለቲካ ጥገኝነት ጠያቂዎቹ የግል ጉዳይ ግን አስተያየት መስጠት አንፈልግም ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያም መንግሥት ለህትመት እስከገባንበት ሳምንቱ መጀመሪያ ድረስ በጉዳዩ ላይ ምንም መግለጫ ሳይሰጥ ቆይቷል። መንግሥት መንገደኞቹ ወደ አገር ተይዘው እንዲመለሱ እየተደራደረ መሆኑን የገመቱ ቢኖሩም የአየር ላንድ መንግሥት ምን እንዳደረገ ወይም ማድረግ እንዳሰበ በቅርብ ጊዜ ውስጥ አልተገለጸም።

የከፋውም የደላውም፣ ፓይለቱም ፣መንገደኛውም በየብስም በውሃም እናም ደግሞ

ዛሬም በአየርም አገር እየጣለ የሚወጣበት ምክንያት ለብዙዎች እንቆቅልሽ እየሆነ ነው። ስደተኞቹ የኢኮኖሚ እንጂ የፖለቲካ ችግር የለባቸውም ሲል የኖረው መንግሥት ኢኮኖሚው አድጓል እየተባለ ባለበትም ቁጥር ሰዎች አገር ጥለው መኮብለላቸው አስገራሚ ይመስላል።

8 የኢትዮጵያ አየር መንገድ መንገደኞች ጥገኝነት ጠየቁ

መንግስት አይ.ኤስ.አይ.ኤስን ለመቃወም በጠራው ሰልፍ ሰበብ እስር ላይ ቆይተው እንዲፈቱ ተወስኖላቸው ከእስር ቤት ሲወጡ እንደገና በፖሊስ ተይዘው የታሰሩት ወንይሸት ሞላ፣ ኤርሚያስ ፀጋዬ፣ ዳንኤል ተስፋዬና ቤትሄልየም አካለወርቅ ላይ ፖሊስ አዲስ ክስ አቀረበ፡፡

እነ ወይንሸት ሰኔ 18/2007 ዓ.ም

ቀደም ብለው ተከሰውበት በነበረው ተመሳሳይ ‹ወንጀል› ፖሊስ የምርመራ መዝገብ ይዞ ቀደም ብለው ውሳኔ ባገኙበት በተመሳሳይ ቄራ ፍርድ ቤት ቀርበው ዳኞቹ ‹‹እኛ ፈርደናል፤ እንዲለቀቁም ወስነናል፣ ከዚህ በኋላ ይህን ጉዳይ አናይም›› በሚል መዝገቡን እንደማያዩ ገልጸው መመለሳቸው ይታወቃል፡፡

ይሁንና ዛሬ ሰኔ 19/2007 ዓ.ም በቄራ መጀመሪያ ፍርድ ቤት ቀርበው ፖሊስ ‹‹ምስክሮችና የምስክሮቹ ጓደኞች ላይ ዛቻና ማስፈራሪያ አድርሰውብኛል›› ሲል ሌላ ክስ አቅርቧል፡፡ ፖሊስ እነ ወይንሸት ሰኔ 15/2007 ዓ.ም በቄራ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት ቀርበው እንዲፈቱ ከተወሰነላቸው በኋላ ፍርድ ቤቱ ግቢ ውስጥ የነበሩትን ምስክሮችና የምስክሮች

Obama is Under fire for visiting Ethiopia page 11

Hammond: Andy Tsege detention ‘undermining UK-Ethiopia

relations page 11

ሰማያዊዎችን ፍርድ ቤት ሲለቃቸዉ ፖሊስ ያዛቸዉጓደኞችን ‹‹ወያኔ ለዘላለም አይኖርም፣ እንገናኛለን፣ ቤታችሁን እናውቀዋለን፣ የወያኔ ተላላኪዎች›› በሚል ዛቻና ማስፈራሪያ አድርሰውብኛል ብሏል፡፡

ሆኖም እነ ወይንሸት በወቅቱ የመሰከሩባቸውን ሰዎች ፍርድ ቤቱ ግቢ ውስጥ እንዳላዩዋቸው፣ ዛቻና ማስፈራሪያም እንዳላደረሱባቸውና ክሱ ሆን ተብሎ እስር ላይ ለማቆየት የተደረገ ነው ብለዋል፡፡

እነ ወይንሸት በአዲሱ ክስም የዋስትና መብት የተከለከሉ ሲሆን በምስክሮችና የምስክሮች ጓደኞች ላይ ዛቻና ማስፈራሪያ አድርሰውብኛል ያለው ፖሊስ ምስክር ለማሰማት ለማክሰኞ ሰኔ 23/2007 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቶታል፡፡ (በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር)

ተገድሏል

የሰማያዊው ፓርቲ ዕጩ ሳሙኤል አወቀ

Model’s split from husband finally made

public page 13

Lemn Sissay announced as next University of Manchester Chancellor page 9

ገጽ 14

ገጽ 5

ባቡር በቻይንኛ ምንድነው? ገጽ 3

አየር መንገዱ ከ2 ነጥብ 6 ቢሊየን ዶላር በላይ ወጪ ስድስት

ተጨማሪ 787 ድሪምላይነር አዘዘ

ቦይንግም ተገላገለ

ይድረስ ለውድ ፕሬዚደንት ዙማ፣

ገጽ 12

32ኛው የኢትዮጵያን ስፖርት በዓል በሜሪላንድ እየተካሄደ ነው

ገጽ 4

ገጽ 2

Page 2: Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 … 92.pdf · Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, ... በቀድሞው

ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ Zethiopia Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com 2

RE

:FU

EL

- Z

ethi

opia

7/1/

2015

9139

295-

IN21

715

AO

NSE

C5.

12”

x 9.

61”

Eri

c M

elle

ndor

f v.

1

Renaissance Hotels is an equal opportunity employer commi ed to hiring a diverse workforce and sustaining an inclusive culture. Marrio Interna onal does not discriminate on the basis of disability, veteran status or any other basis protected under federal, state or local laws.

A place in the world with style like yours. Great benefi ts, training, opportunities for career growth and promotion.

Bring your whole self to work. As an ambassador at the world’s leading lifestyle brand.

Explore opportunities that fi t your style atwww.renhotels.com/careers Search by Job #.

Renaissance Arlington Capital View, 2800 South Potomac Ave, Arlington, VA 22207, is currently hiring for the following positions:

PM Cook - Job #15000G45Cook - Job #15000OBQBQT Cook - Job #15000WTBPM Cook - Job #15000WT5Station Attendant - Job #15000WT5

BECAUSE OUR BRAND IS YOUR STYLE.የጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ አማካሪ አቶ አርከበ እቁባይ

ግንቦት 20ን አስመልክቶ ከዘመን መጽሔት ጋር ቆይታ አድርገዋል። ከቀረበላቸው ጥያቄ መካከል ድርጅትና መንግሥታቸው ኤርትራንም ሆነ ወደቡንም አሳጥቶናል የሚሉ ወገኖች አሉና ለእነዚህ ወገኖች ምላሽዎ ምንድን ነው? የሚለው አንደኛው ነበር። እንዲህ ብለው መለሱ-

“ስለ ሕዝብ የማያነሳና የማያስብ ግለሰብ ወይም ቡድን ብቻ ነው ስለ መሬትና ወደብ የሚያነሳው። አገር ማለት ሕዝብ ነው። ስለሆነም ስለ ሕዝቦች በምናስብበት ጊዜ የኤርትራ ሕዝብ እንደ ሕዝብ ነው መወሰድ ያለበት።” በማለት የጀመሩት አርከበ ስለ ኤርትራ ህዝብ ፍላጎትና ስለድርጅታቸው አቋም እንዲህ ብለዋል “ የኤርትራ ሕዝብ ምን ይፈልጋል? ለብዙ ዓመት በጦርነት ውስጥ የቆየ ሕዝብ ነው፤ ከ30 ዓመታት በላይ። ከኢትዮጵያ መገንጠል እንፈልጋለን አሉ። 99 በመቶ የሚሆነው የኤርትራ ሕዝብ ነፃ ኤርትራን እንፈልጋለን አለ። ሕዝቡ ፍላጐቱን በድምፅ አረጋገጠ ማለት ነው። የሕዝቡ ፍላጐት ደግሞ መሟላት አለበት። ዴሞክራሲ ማለት ለሕዝብ መቆም ማለት ነው። ማነው የመጀመሪያ አገር ኤርትራን እንደ አገር የተቀበለው? የኢትዮጵያ መንግሥት ነበር። ያ ሆኖ ሰላም ማረጋገጥ ተችሏል። ስለዚህ ያንን ያደረግነው ከሰላም፣ ከዴሞክራሲ፣ ከሕዝቦች መብት ማረጋገጥ አንፃር ነውና ይሔ መሆኑ ተገቢ ነው።”

ወደብን አስመልክቶ ግን አቶ አርከበ የሰጡት ማብራሪያ “የአሰብን ወደብ (ባለመጠቀም) የግመል መጠጫ ሆኖ ይቀራል (እናደርገዋለን?) በማለት ዝተው ከነበሩት ከአቶ መለስ ዜናዊ ንግግር ጋር የሚመሳሰል ይመስላል። “እኛ ወደብ መች ቸገረን?” ያሉት አቶ አርከበ ወደብ ብቻውን ልማትን የማያስገኝ መሆኑን በመግለጽ ጥያቄውንም ሆነ ባለወደቢቷን ኤርትራን ከሶማልያ ጋር በመደመር ያናናቁ መስለዋል። እንዲህ ብለዋል-

“ግን ዋናው ነጥብ ምንድንነው ወደብ ልማት ያመጣል ብለው የሚያስቡ ሰዎች ስለ ኢኮኖሚ ልማት ምንም የማይገባቸው ሰዎች ናቸው። በአካባቢያችን ሠፋፊ ወደብና የባህር ዳርቻ ያላቸው አገሮች እነማን ናቸው? አንዷ ሶማሊያ ናት። ሁለተኛዋ ማናት? ኤርትራ ናት። ሁለቱንም እንያቸው በጥፋት ሂደት ያሉ አገሮች ናቸው። ሶማሊያ ግን አሁን በተሻለ እንቅስቃሴና

መረጋጋት ውስጥ ናት። ኢኮኖሚ ልማት በእነዚህ አገራት የለም። ስለዚህ ልማትና ዕድገትን የሚያመጣው ወደብና የባህር ዳርቻ ነው የሚለው አስተሳሰብ ሕዝብን እንደ ሕዝብ ያለ ማየት አስተሳሰብ ምንጭ ነው። እኛ ወደብ መች ቸገረን? በጂቡቲና በበርበራ መጠቀም እንችላለን። የኤርትራም ሁኔታ መቀየሩ አይቀርም፡፡ አሁን ያለው ሁኔታ ለዘለዓለም ይኖራል ብለን አንገምትም። በእኔ ግምት በሚቀጥሉት አስር ዓመታት ውስጥ ለውጥ ይመጣል ባይ ነኝ። የኤርትራን ወደብ እንጠቀማለን። የኬንያን ወደብ መጠቀም እንችላለን። ከዚያ ወደ ኢትዮጵያ የሚገባ መስመር ለመገንባት ታቅዷል። የሱዳንንም እንጠቀማለን። ቢቻል ወደብ ቢኖረን ጥሩ ነበር ግን የሁሉም መቋጫና መፍትሔ እርሱ ነው ማለት አይደለም። የሚያመጣው መሠረታዊ ለውጥም የለም በእኔ እምነት።”

ወደብ ልማት ያመጣል ብለው የሚያስቡ ሰዎች ስለ ኢኮኖሚ ልማት ምንም የማይገባቸው ሰዎች ናቸው ኤርትራና ሶማልያን እይዋቸው!

አቶ አርከበ እቁባይ

አየር መንገዱ ከ2 ነጥብ 6 ቢሊየን ዶላር በላይ ወጪ ስድስት ተጨማሪ 787 ድሪምላይነር አዘዘ

ቦይንግም ተገላገለ ሰሞኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ2 ነጥብ 6 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ ወጪ ስድስት ተጨማሪ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላኖችን ማዘዙን አስታውቋል። ይህም የ787 ድሪምላይነር አውሮፕላኖቹን ቁጥር 19 ያደርስለታል።

የአየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም እንደገለጹት፥ አዲስ የታዘዙት ድሪምላይነር አውሮፕላኖች የአየር መንገዱን አቅም በማሳደግ የሚሰጠውን አገልግሎት ምቹ እና አስተማማኝ ያደርጉታል።

የቦይንግ የንግድ አውሮፕላን ፕሬዚዳንት እና ዋና ስራ አስፈጻሚ ሬይ ኮነር በበኩላቸው፥ አየር መንገዱ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ1960 ጀምሮ የቦይንግ ደንበኛ መሆኑን አስታውሰዋል። የ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላንም በርካታ መዳረሻዎች ላሉት እና ብዙ ሺህ ኪሎሜትሮችን ለሚጓዘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚገባ ነው ማለታቸው ተዘግቧል።

787 ድሪምላይነር አውሮፕላን ለተጓዦች ከሚሰጠው ምቾት ባሻገር በዝቅተኛ የነዳጅ ፍጆታው

እና አነስተኛ የበካይ ጋዝ ልቀቱ ይታወቃል።

ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላንን በመጠቀም ከአፍሪካ ቀዳሚ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ወቅት ቦይንግ 737፣ 757፣ 767፣ 777 እና 787 አውሮፕላኖችን ለተጓዦች ቦይንግ 757፣ ኤምዲ11፣ 777 እና 737-

400ኤፍ አውሮፕላኖችን ደግሞ ለጭነት አገልግሎት እያዋላቸው ይገኛል።

በሌላ ዘገባ ደግሞ በተደጋጋሚ እክሎችና ብልሽቶች ሲተች የቆየው ቦይንግ፣ 788 ድሪም ላይነር አውሮፕላኖቹን፣ ለረጅም ጊዜ፣ (ዘገባዎች እንደሚሉት እስከ አምስት ዓመት) በገበያ ላይ ቆይቶ ገዢ ያላገኘበት ሁኔታ ተፈጥሮ ነበር። በዚህ ሁኔታ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግዢዎቹን መፈጸሙ ለአየር መንገዱ የላቀ ጠቀሜታ ቢኖረውም ለቦይንግም እንዲሁ ትልቅ እፎይታን የፈጠረ መሆኑ ተዘግቧል።

ዋሽንግተን ዲሲ ኮንቬንሽን ሴንተር አጠገብ ጥሬ ሥጋ - ክትፎ- ጥብስ - የበግ ወጥ -የጾም በዓይነቱ

ቁርስ ምሳ ራት ከጧቱ 9 ሰዓት

ጀምሮ ክፍት ነው

በዘንድሮው 32ኛው የሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያውያን የስፖርት በዓል ላይ እንደታየው ኳስ ሚዳው የአገርም ሜዳ ነው። እንኳን ከየቦታው ክየስቴቱ የመጡትን፣ እዚሁ ዋሽንግተን አካባቢ አብረው በየአደባባዩ የሚውሉቱንም ያነፋፍቃል ያሳስቃል!- የኢቲዮ ቱብ ልጆች እንዲህ ያለውን ትዝታ እየተከታተሉ በካሜራቸው ያስቀራሉ - ፎቶ ኢትዮቱብ

Page 3: Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 … 92.pdf · Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, ... በቀድሞው

ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ Zethiopia Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com 3

በኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን እየተተገበሩ ያሉት የሃዲድ መስመር ዝርጋታዎች በውሉ መሰረት እየተከናወኑ መሆናቸውን ለማረጋገጥና የጥራት ደረጃቸውን ለመከታተል የሚያስፈልጉ ሰነዶችን ተቋራጮቹ ከቻይንኛ ወደ እንግሊዝኛ አስተርጉመው ለማቅረብ ባለመፈለጋቸው በሥራው ላይ እንቅፋት መፍጠሩ ተገልጿል፡፡

የፌደራል ዋናው ኦዲተር ባቀረበው ሪፖርት ላይ እንደተገለፀው፤ ሁሉም የባቡር ፕሮጀክቶች :- የአዲስ አበባ ከተማ ቀላል ባቡር ፕሮጀክት፣ የአዲስ አበባ ሰበታ ሜኤሶና የሜኤሶ ደዋሌ ፕሮጀክቶች የባቡር ግንባታዎች በቻይና የሃዲድ ግንባታ ደረጃ 2 እየተሰሩ መሆናቸው ቢገለጽም ተቋራጮቹ የጥራት ማረጋገጫ ማኑዋል፣ የላብራቶሪ ቁሳቁስ ማኑዋልና የዋና ዲዛይኑን ሰነድ የእንግሊዝኛ ትርጉም ለማቅረብ ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡

በአዲስ አድማስ መታሰቢያ ካሳዬ እንደተዘገበው ኮርፖሬሽኑ አገራዊ የባቡር ምህንድስና እና የዲዛይን ኮዶች አዘጋጅቶ ተግባራዊ ማድረግ ሲገባው የተለያዩ የውጭ አገር የባቡር ስታንዳርዶችን የተከተሉ የዲዛይንና ግንባታ ስምምነቶችን መፈረሙም

በሪፖርቱ ላይ ተጠቁሟል፡፡ በኮርፖሬሽኑ እየተተገበሩ ያሉት የመሠረተ ልማት ግንባታዎች በ1999 ዓ.ም በትራንስፖርት ሚኒስቴር መሪነት አጥኚ ግብረሃይል ተቋቁሞ፣ አማራጭ የየብስ ትራንስፖርትን አስመልክቶ ያደረገው ጥናት እንጂ እያንዳንዱን ፕሮጀክት አስመልክቶ የተሰራ የፕሮጀክት ጥናት ሰነድ እንደሌለም ተገልጿል፡፡

በሜኤሶ ደዋሌ የባቡር መስመር ግንባታ ላይ ያለውን የእሳተ ገሞራ መከሰት ሁኔታ ሊገመግም የሚችል ጥናት አለመደረጉን የጠቆመው ሪፖርቱ፤ ኮርፖሬሽን እ.ኤ.አ በ2011 ከቻይናው ተቋራጭ (CCECC) ጋር ባደረገው ውል፣ ተቋራጩ ባቀረበው የቴክኒክ ፕሮፖዛል ውስጥ በምስራቅ አፍሪካ ያለው የእሳተ ጐሞራ በዓመት 0.5 ሳ.ሜ እንደሚሰነጠቅ ጠቁሞ ይህ ትልቅ ስምጥ ሸለቆ አሁንም እየተሰነጠቀ መሆኑንና በዚህ ምክንያትም በላይኛው የምድር አካባቢ ያለው ክፍል ላይ ከፍተኛ እንቅስቃሴ

መኖሩን፣ በተደጋጋሚ ፍንዳታዎችና የመሬት መሰንጠቆች እየተከሰቱ እንደሆነ ተነግሯል። ነገር ግን ኢትዮጵያ ውስጥ በዝርዝር የተጠናና የሚታወቅ ነገር ባለመኖሩ የእሳተ ጐሞራ መከሰት ሁኔታን አስተማማኝ ለማድረግ አለመቻሉን ኦዲት ሪፖርቱ ይፋ አድርጓል፡፡

በኮርፖሬሽኑ እየተተገበሩ ባሉ ፕሮጀክቶች፣ የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ተግባራዊ

እየተደረገ አይደለም ያለው ሪፖርቱ፤ በአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ በርካታ የቱሪስት መተላለፊያ መንገዶችን ሳያስፈቅዱ መዝጋት፣ የፓርኩን ንፅህና አለመጠበቅ ያለፈቃድ መንገዶችን በፓርኩ ውስጥ እየቀደዱ ማውጣት የመሳሰሉ ችግሮች እንደሚከሰቱ ጠቁሞ በፕሮጀክቶቹ ላይ የሚሰሩ የውጪ አገር ባለሙያዎች የዱር እንስሳትን ያለፈቃድ እያደኑ ለምግብነት እንደሚያውሉም ገልጿል፡፡ (አዲስ አድማስ)

ባቡር በቻይንኛ ምንድነው?ቻይኖቹ የባቡር ፕሮጀክቶቹን ሰነድ ከቻይንኛ ወደ እንግሊዝኛ አንተርጉምም አሉ - አማርኛውስ እሺ ይቅር እንግዝሊኛውን እንኳ ግን እንዴት.....?!!

በቀድሞው ብሥራተ ወንጌል ሬዲዮ ጣቢያ፣ በአብዮታዊት ኢትዮጵያ ድምፅ ዓለም አቀፍ አገልግሎት፣ በኢትዮጵያ ሬዲዮና በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በጥቅሉ ለ30 ዓመታት ያገለገለው ዳርዮስ ሞዲ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ሰሞኑን በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ሲዘገብ ቆይቷል። ሪፖርተር እንደሚከተለው ጽፎታል።

ዳርዮስ ሞዲ በትውልዶች መካከል ጎልቶ የሚታወቅ ስም ነው፡፡ በሬዲዮ ጋዜጠኛነቱ በተለይም ከ20 ዓመታት በላይ ባስቆጠረው የዜና አንባቢነቱ የአድማጮችን ቀልብ በሚገዛው ነጐድጓዳማ ድምፁ የሚታወስ ጎምቱ ጋዜጠኛ ነበር፡፡

ዳርዮስ በብዙኃኑ አድማጮች ዘንድ ከልሂቅ እስከ ደቂቅ የሚታወስበት አጋጣሚ የቀድሞው መንግሥት ፕሬዚዳንት የነበሩት ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማርያም አገር ጥለው መሄዳቸውን የገለጹበት የግንቦት 13 ቀን 1983 ዓ.ም. ዕለተ ማክሰኞ ዜናው ነበር፡፡

በቀድሞው ብሥራተ ወንጌል ሬዲዮ ጣቢያ፣ በአብዮታዊት ኢትዮጵያ ድምፅ ዓለም አቀፍ አገልግሎት፣ በኢትዮጵያ ሬዲዮና በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በጥቅሉ ለ30 ዓመታት ያገለገለው ዳርዮስ ሞዲ ድምፁ አሁን የለም፡፡ በአፀደ ሥጋ ተለይቷል አርፏል፡፡

የቤተ መንግሥት ፎቶ አንሺና የፎቶግራፍ ቤት ከነበራቸው ከፋርሳዊ (ኢራን) አባቱና ከኢትዮጵያዊት እናቱ በአዲስ አበባ ከተማ ራስ መኰንን ድልድይ አካባቢ በ1938 ዓ.ም.የተወለደው ዳርዮስ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ያጠናቀቀው በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት ነበር፡፡

በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ ትምህርቱን መከታተል ቢጀምርም በወቅቱ በነበረው የተማሪዎች ንቅናቄ ሳቢያ ጓደኛው የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ማኅበር ፕሬዚዳንት የነበረው ጥላሁን ግዛው መገደልን ተከትሎ ትምህርቱን ማቋረጡን ገጸ ታሪኩ ያመለክታል፡፡

በመካነየሱስ ቤተ ክርስቲያን ሥር የነበረውና በዓለም ሉተራን ፌዴሬሽን በሚረዳው የዘመኑ ታዋቂ የሬዲዮ ጣቢያ ብሥራተ ወንጌል ሬዲዮ በ1964 ዓ.ም. በመቀጠር ጣቢያውን ደርግ እስከ ወረሰበት ጊዜ ድረስ ሠርቷል፡፡ ድኅረ አብዮት በአብዮታዊት ኢትዮጵያ ድምፅና በብሔራዊ ሬዲዮ እስከ 1980ዎቹ መገባደጃ ድረስ በዜና አንባቢነት፣ በፕሮግራም አዘጋጅነት የሠራ ሲሆን፣ ጡረታ እስከወጣበት 1994 ዓ.ም. ድረስ ያገለገለው በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የውጭ ቋንቋ ዴስክ ነበር፡፡

ስለዳርዮስ ሙያ ከዓመታት በፊት ይታተም በነበረ አንድ መጽሔት ላይ አስተያየት የሰጠው ዓለምነህ ዋሴ፣ ‹‹ዳርዮስ ከፍተኛ የትርጉም ችሎታ አለው፤ ቃላትን መፈብረክም ይችልበታል፡፡ ዛሬም ድረስ በሬዲዮ የምንሰማቸው ሙያዊ ቃላት በርካቶቹ የርሱ ፋብሪካ ውጤቶች ናቸው፡፡

በዘመነ ደርግና በኢሕአዴግም መንግሥታዊ መግለጫዎችንና አዋጆችን ከሚያቀርቡት አንዱ የነበረው ዳርዮስ ሞዲ ከሁለት ዓመታት ወዲህ ባደረበት ሕመሙ ሕክምናውን ሲከታተል የቆየው ዳርዮስ ያረፈው ሰኔ 13 ቀን 2007 ዓ.ም. ሲሆን፣ ሥርዓተ ቀብሩ በጉራራ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሰኔ 1 ቀን ተፈጽሟል፡፡

ጋዜጠኛ ዳርዮስ ባለትዳርና የሰባት ልጆች አባት ነበር፡፡

ጋዜጠኛ ዳርዮስ ሞዲ አረፈ

ምርጫው የተካሄደውም ከ150 በላይ የዩኒቨርስቲው ሰራተኞች፣ የቀድሞ ሰራተኞችና ተማሪዎች እንዲሁም የጠቅላላው ጉባኤ አባላትም በተገኙበት ነው፡፡ ለዕጩ የቀረቡት የሃሌ ሙዚቃ ዳይሬክተር ማርክ ኢልደር፣ የቀድሞ የካቢኔ ሚንስትር ፒተር ማንደልሰንና ለምን ሲሳይ በግጥም ተሸላሚዎች ሲሆኑ ከሚያዚያ ወር ጀምሮ ለዩኒቨርስቲው ሃላፊነት ቦታ እየተወዳደሩ ነበር።

በውድድሩ የመጨረሻ ውጤትም ኢትዮጵያዊው ለምን አሸናፊ በመሆኑ የሃላፊነት ቦታውንም ለ7 ዓመት ከያዘው ከቶም ብሎክስ ሃም ተቀብሎ ከመጪው ሐምሌ 25 ጀምሮ ሥራውን እንደሚጀምር ይጠበቃል። በጥቅምት ወር ደግሞ በዩኒቨርስቲው ውሰጥ ዝግጅት ይካሄዳልም ተብሏል።

ኢትዮጵያዊው ለምን በሳውዝ ባንክ ማዕከል ተባባሪ አርቲስት፣ በሌተር ቦክስ ክለብ ድጋፍ ሰጪ እንዲሁም በፋውንድሊንግ ሙዚየም ባልደረባ እንደሆነ ተገለጿል።

ኢትዮጵያዊው ገጣሚና የትያትር ደራሲ ለምን በበኩሉ ‘’የመጀመሪያ አላማዬ ሰዎችን ማትጋትና እኔም መትጋት ነው ‘’ብሏል።

‘’የዛፍ ጫፍ ላይ ለመድረስ የመጀመሪያው ቅርንጫፍ ላይ ትወጣለህ ነገር ግን ኮኮቦች ላይ ለመድረስ ዛፎቹ አናት ላይ ትወጣለህ’’ሲልም ተናግሯል።

የዩኑቨርስቲ ሃላፊነተ/ ቻንስለርነት/ የሥራ ጊዜው ሰባት ዓመት ሲሆን የጠቅላላ ጉባኤውን ስብሰባ እንደሚቆጣጠርና ዩኒቨርስቲውን በተለያዩ መድረኮች ወክሎ በመገኘት የአምባሳደር ሚና እንደሚኖረው ከዩኒርስቲው ድህረ-ገጽ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ብዙ መጽሐፎቹን የጻፈ ሲሆን፣ ከእነዚህም ውስጥ ቴንደር ፊንገርስ ኢን ኤ ክሌንችድ ፊስት፣ ሪቤል ዊዝአውት አፕላውዝ፣ ሞርኒንግ ብሬክስ ኢን ዘ ኤሊቬተር፣ ዘ ፋየር ፒፕል፣ ሊስነር፣ ዘ ኢምፐረርዋች ሜከር ይጠቀሳሉ፡፡ እነዚህ ሥራዎች የተለያዩ ሽልማትንና ተደናቂነትን አግኝቶለታል፡፡

ኦርደር ኦፍ ዘ ብሪትሽ ኢምፓየር አባል መሆን የቻለ ከጥቂት ተጠቃሽ ገጣሚዎች ውስጥ ለምን አንዱ ነው፡፡ ከገጣሚነቱ በተጨማሪ ጸሐፌ ተውኔትም ነው፡፡ ሃምሳኛውን የአፍሪካ ኅብረት አከባበር አስመልክቶ በብሔራዊ ቴያትር ሥራውን ያቀረበ ሲሆን፣ ብዙዎችን ከመቀመጫቸው ያስነሳ ያስደሰተ ዝግጅትም አቅርቦ ነበር ፡፡

ቤተሰቦቼንና ታሪኬን በማግኘቴ ራሴን አግኝቼያለሁ፡፡ እናም ራሰን እንደገና ከመፍጠር ይልቅ በተማርኩት ውስጥ አድጌያለሁ፡፡ በዚህ ጉዞ ላይ በመሆን የተመረቅኩ መስሎ ይሰማኛል፡፡ ግጥሞቼም የዚህ ጉዞ ውጤት ነው፡፡ የአድዋ ጦርነትም የራሴን ይሄንን ኃይል ያለውን ታሪክ ያወቅኩበት ነው፡- ብሏል።

ታሪኩን፣ ደስታ ስቃዩን፣ ጥበበሥላሴ ጥጋቡ፣ ኢትዮጵያ ላይ አግኝቶት በቃለ መጠይቁ ውብ አድርጎ አጫውቶታል። ለምሳሌ እንዲህ ብሎ ጠይቆታል፦

- እንግሊዝ ተወልደህ አድገህ በኋላም ስለ ኢትየጵያዊ ማንነትህ ማወቅህ ቤትህን የት ያደርገዋል?

ቤተሰቦቼን በመላው ዓለም ነው ያገኘኋቸው እናም የተረዳሁት ነገር ቢኖር እኔ የተገኘሁበት ሁሉ ቤቴ ነው፡፡ ቤቴ እኔ ውስጥ ነው ቤተሰቦቼን ሳገኝ የተረዳሁት ነገር ቢኖር ራሴንም ማግኘቴን ነው፡፡ ብዙ ቤቶች አሉኝ፡፡ ኢትዮጵያ ግን ለየት

ያለና ተወዳጅ ስፍራዬ ነው፡፡ ዕድለኛም የሆንኩ ይመስለኛል፡፡ ከነዛ ሁሉ አገራት ከአንዱ አገር መሆን ስችል ከዚህ ጠንካራ፣ ኩሩ፣ ታሪኳ ጠቃሚ ከሆነ አገር በመገኘቴ ያስደስተኛል፡፡ የሰው ዘር መገኛም ሉሲ እዚህ ነች፡፡ ኢትዮጵያ በአፍሪካም ይሁን በዓለም ታዋቂ ከሆኑት አገራት ውስጥ አንዷ ነች፡፡

ለምን ጥያቄውን መመለሱን ይቀጥላል.... ወደ ኢትዮጵያ የመጣው ለሰባተኛ ጊዜ መሆኑን ከገለጸ በኋላ አመጣጡን ሲያስረዳ

ለመጀመሪያ ጊዜ የመጣሁት ከ18 ዓመት በፊት ነው፡፡ ይሄም አባቴን የመፈለግ፣ ጉዞ ጊዜ ሲሆን፣ ከቢቢሲ ጋርም አንድ ጥናታዊ ፊልም ሠርቼያለሁ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁሉም ደስተኛ ነው፡፡ ሁሉ ነገር ለየት ያለ ነው፡፡ ኢትዮጵያዊ ሆነህ ኢትዮጵያ ውስጥ ስትመጣና እዚህ መጥተህ የማታቅ

ከሆነ ነገሮች እንዲገቡህ ብዙ ጊዜ መምጣት አለብህ፡፡ እዚህ መጥተህ ነገሮችን እንደምታቅ ማስመሰል የለብህም ማዳመጥ፣ ከመፍረድ መቆጠብ እንዲሁም እንዲገባህ መሆን አለበት፡፡ የኢትዮጵያን ታሪክ ለራሳቸው ጥቅም ሲባል ታሪኳ ዕምነት፣ ባህል፣ ጥበብን በተመለከተ ሲጣመም ኖሯል፡፡ ስለ ታዋቂው ሠዓሊ አፈወርቅ ተክሌ ሳወራ ብዙዎች ስለሆነ ስለማያቁት ምስጢራዊ አርቲስት የማወራ ይመስላቸዋል፡፡ እሱ ማለት በዓለም ደረጃ ታዋቂ፣ ታሪኩም ጠቃሚ ብዙ የተባለለት አርቲስት ነው፡፡ እንደውም ብዙ ለንደን ከማቃቸው አርቲስቶች በላይ ብዙ የተባለለት ነው፡፡ ነገር ግን ነገሮችን እኛና እነሱ በሚል ሁኔታ አላየነውም (አልከፋፍለውም) እንደሚሰማኝ ከሆነ በማየውና ነገር ሕይወቴ እየጨመረና እየተቀየረ ነው፡፡ ካለበለዚያ ግን ተቃራኒ የመሆን ጉዳይ ነው የሚሆነው ሁልጊዜም ራስህን የምታይበት ወይም ደግሞ ራስህን የምትገልፅበት መንገድ በማትወደው ወይም በምትቃረነው መንገድ ከሆነ ምን እንደምትደግፍ ማወቅ አይቻልም፡፡ ራስህን የምትገልጽበት መንገድ በምትደግፋቸው ነገር ከሆነ ራስህን መረዳትም ሆነ ማወቅ ይቻላል፡፡ ለኔ ከኢትዮጵያ ጋር ያለኝ ግንኙነት የሕይወት ጊዜ ረጅም ግንኙነት ነው እናም ያስደስታል፡፡

አባትህን ለማወቅ ያደረግከው ጉዞ እንዴት ነበር? ተብሎ ተጠየቀ።

አባቴ እ.ኤ.አ በ1974 በአዲስ ዓመት በአውሮፕላን አደጋ ሕይወቱ አልፏል፡፡ ፓይለት ነበር፡፡ ለባለቤቱ ለአልማዝ የሆኑ ሰዎችን ጐንደርና አስመራ ደርሼ እመጣለሁ እናም በሰዓታት ውስጥ እመለሳለሁ ብሎ ሄደ ግን በሚያሳዝን ሁኔታ የሰሜን ተራሮች ላይ አውሮፕላኑ ተከስክሶ ሞተ፡፡ ከሞተ ከሃያ ዓመታትም በኋላ የአውሮፕላኑን ክስካሽ አገኘሁት፤ ተራራው ጫፍ ላይ ጥግ ስብርባሪዎች አሁንም አሉ የሚያስገርም ነው፡፡ መጀመሪያ ሲታይ አረንጓዴ ይመስላል ግን በደንብ ሲታይ

ግራጫማ መሆኑ ያስታውቃል፡፡ ስብርባሪው ላይ ዛፎች፣ ቁጥቋጦዎች፣ በቅለውበታል እንዲሁም ከበውታል፡፡ ሰዎች ከሞቱ በኋላ ስለነሱ ብዙ ነገር ትማራለህ፡፡ ምክንያቱም ብዙ ሰዎች ስለነሱ

የሚሰጡት ምስክርነት ተስሎ አንድ ስዕል ይወጣል፡፡ ይሄ ምን ማለት ነው አንድ ሰው ብርሃን እያንፀባረቀ ነው ይሄ ብርሃን በደመና ላይ ባለው ላይ ባለ አቧራ የሰው ምስልን ያሳያል፡፡ ማየት ይቻላል ሊጨበጥ ግን አይችልም ይለናል በ360 ዲግሪ ዙሪያውን ማየት ይቻላል፡፡ ብዙዎች ቤተሰቦቻቸውን በዛ መልክ ለማየት አይችሉም፡፡ ስጦታ እንደተሰጠኝ ያህል ነው የምቆጥረው ምክንያቱም አባቴን እያንዳንዷ ነጥብ

ቢሊዮን ሆኖ ተሰባስቦ አንድ ምስል ሰጥተውኛል፡፡ እነዚህ ነጥቦች የሰዎች ምልክታ ናቸው፡፡ እነዚህ የምስሎች ቁርጥራጭ ምልከታዎች የአባቴን ምስል ግልፅ አደረጉት እናም ለዚህም ነው ተመርቄያለሁ የምለው፡፡

ለምን ሰቆቃና ንዴት!

የልጅነት ጊዜ ሰቆቃ የተሞላበት ነው፡፡ በአሳዳጊ ቤተሰቦቼ ጥቃት ደርሶብኛል በተለያዩ ማደጎ ቤቶች ተወርውሬያለሁ፡፡ እስከ አስራ ስምንት ዓመቴ ድረስ በጣም ከባድ አስቸጋሪና በእንግልት የተሞላ ነበር፡፡ ያደግኩበት ሁኔታ ከዝቅተኛ በታች በጣም በዝቅተኛ ሁኔታ ነበር፡፡ ያ ከዝቅተኛ በታች ያለው ያ ዝቅተኛ ልጅ ነበርኩ፡፡ በሰዎች አፍሪካዊ ልጅ ማለት ምን ማለት ነው የሚል ጥቃት ደርሶብኛል በዛ በሕመም፣ በአደገኛ ሁኔታ ባሳልፍም ምሬት የለብኝም፡፡ ምሬት የተሸከመውን ማህደር ይንደዋል፡፡ ሕመምን፣ ንዴትን ካላስታመምከውና ካልመረመርከው መፍትሔ ካልሰጠኸው ዝም ብሎ ከተደበቀ ሰውን ያፈራርሳል፡፡ መናደድ ምንም ማለት አይደለም ግን ንዴት ጥያቄ ይጠይቃል፡፡ ያ ጥያቄ በትክክለኛ ሁኔታ መመለስ አለበት፡፡ እንደማምነውም ንዴት ፍቅርን ለመፈለግ የሚደረግ የመግለጫ ዘዴ ነው፡፡ ብዙ የሚናደዱ ሰዎች በሕይወታቸው የሌለውን ፍቅር እየፈለጉ ስለሆነ ነው ንዴት ከፍተኛ ስሜት ነው፡፡ አንድ ሰው አማኝ ከሆነ ንዴት ማለት ኢየሱስ ምኩራብ ውስጥ የሸቀጥ ዕቃዎችን እንዲበታትን ያደረገው ስሜት ነው ወይም ደግሞ ቃየል እንዲሠራው ያደረገውን ስህተት ያሠራው ስሜት ነው፤ ማለት ይቻላል፡፡ ንዴትን በምን ዓይነት መንገድ ነው የምታየው ወይም የምትጋፈጠው የሚለው ጠቃሚ ነው፡፡ አንዳንዶች ንዴታቸውን ይክዱታል፡፡ ይሄም አደገኛ አካሄድ ነው፡፡ ሁሉንም ጥያቄዎችን መልሻቸዋለሁ ለምን እነዛ ማደጐ ቤቶች ውስጥ እንደነበርኩ? እናት ለምን እንዳልነበረኝ? እነማን

እንደሆኑ? ማን እንደዋሸኝ ጭምር፡፡

ስሙ ለምን ነው። ለምን?

ሁልጊዜም ይፋ የሆነው ስሜ ለምን ሲሳይ ነው፡፡ ግን እነሱ ኖርማን አሉኝ፤ እኔም እንግሊዛዊነቴን ተቀብዬ ኖርማን ነው ብዬ ተቀብዬ ነበር፡፡ ከሕፃንነቴ ጀምሮ እየተነገረኝ ያደግኩት አፍሪካ አደገኛ ቦታ እንደሆነ ነው፤ የሚገርመው ግን እነሱ ያደጉበትን ማየቴ ነው፡፡ በተለያዩ ነገሮች ራሳቸውን ቀባብተው (ደባብቀው) ይመጣሉ፡፡ አፍሪካን የሚያዩበት ወይም የሚያሳዩበትም ሁኔታ ውሸት ነው፡፡ ይሄንን ሲጋፈጡና እውነታውን ሲያወጡ ነው ከአፍሪካውያን ጋር ጥሩ ግንኙነት የሚኖራቸው፡፡ ስለ ስሜ ማወቄ እውነት እንዲገለጽ አድርጎልኛል፡፡ ሁልጊዜም ተዋሽቼ ነበር፣ ይሄ ስህተት ነው፡፡ ስሜን ካገኘሁ በኋላ የእናቴን የልደት ወረቀት አገኘሁ፡፡ ከዚያም ቤተሰቦቼን መፈለግ ጀመርኩ፡፡

ለምን አዘነ!

“በሕይወቴ ውስጥ በብዙ ተፅዕኖዎች ውስጥ አልፌያለሁ ብዙ ማንነት አለኝ፡፡ ኢትዮጵያዊ ነኝ አማርኛ አልችልም፡፡ እዚህ (ኢትዮጵያ) ኖሬ አላውቅም፡፡ አንድ እህት ብቻ ነው እዚህ ያለኝ፣ የተወሳሰበ ነገር ነው፤ ግን ምንም ማለት አይደለም፡፡ ሰው ማለት የተወሳሰበ ፍጡር ነው፡፡

ላሊበላ እየተራመድኩ ነበር፣ አንድ ዲያቆንም አካባቢውን ያሳየኛል፡፡ ከዚያም ምን እንደምሠራ ጠየቀኝ፣ ገጣሚ ነኝ አልኩት፡፡ በዕውቀቱ ሥዩምን እንደሚያውቀው ነገረኝ፡፡ ከዚያም ከእሱ ጋር አብረን ብሔራዊ ቴያትር ግጥም እንዳቀረብን ነገርኩት፡፡ ከዚያም ስለ ኤፍሬም ሥዩም ነገረኝ፤ በመቀጠልም ከጓደኞቹ ስለ አንድ እንግሊዛዊ ገጣሚ እንደሰማ ነገረኝ፣ እሱ ሳይሆን እኔ ነኝ የተደነቅኩት በጣም ነው የገረመኝ፡፡ ኢንፎርሜሽን የሚጓዝበት መንገድ በኢትዮጵያ መንፈስ ገባሮች አድርጎ እዚህ ላሊበላ ቤተ ክርስቲያን መድረሱ ይገርማል፡፡ ከዓመት በፊት ብሪትሽ ካውንስል ግጥም አቅርቤ ነበር፡፡ እናም አፈወርቅ ተክሌ እራት ጋበዙኝ፡፡ ከዚያም ከሳምንት በኋላ ሞቱ፡፡ በጣም ዕድለኛ ነኝ፡፡

(ምንጮቹ የተቀናበሩት ከቢቢሲ ሪፖርተርና ኢዜአ ናቸው።)

የማደጎው ልጅ ኢትዮጵያዊው ለምን ሲሳይ የእንግሊዝ የማንቺስተር ዩኒቨርስቲ ቻንስለር ሆኖ ተመረጠ

Page 4: Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 … 92.pdf · Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, ... በቀድሞው

ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ Zethiopia Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com 4

በ8 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ እስከ መዝጋት የሚደርስ እርምጃ ተወሰደትምህርት ላይ የነበሩ ተማሪዎችስ እጣ ምን ይሆናል?መንግሥት እያሽቆለቆለ ያለውን የትምህርት ጥራት ለማሻሻል በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ ድንገተኛ እርምጃ መውሰድ መጀመሩን አስታውቋል። በዚህም መሠረት ከተቀመጠው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከምዝገባ (ቅበላ) መስፈርት ውጭ መዝግበው ሲያስተምሩ የተገኙ ስምንት የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ እስከ መዝጋት የሚደርስ እርምጃ መውሰዱን ገልጿል። ኮሌጆቹ ከህግ ውጭ የሆኑ ተማሪዎቻቸውን እንዲያሰናብቱ ህጋዊ የሆኑትን ደግሞ እውቅና ፍቃድ ወዳላቸው ተቋማት እንዲያዘዋውሩ ማድረጉንም አስረድቷል።

የከፍተኛ ትምህርት ጥራትና አግባብነት ኤጀንሲ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ታረቀኝ ገረሱ ሰሞኑን እንደተናገሩት መንግሥት እርምጃውን የወሰደው ባካሄደው ድንገተኛ ግምገማ ነው። ህገወጥ ተግባራት እየፈጸሙ ነው ካላቸው ተቋማት መካከል ናይል፣ ራዳና ሚሽከን ኮሌጆች ፍቃዳቸው ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ እንዲሰረዝ ተደርጓል፡፡ ናይል ኮሌጅ በ2003 ዓ.ም ኤጀንሲው ባደረገው የብቃት ምዘና በመቐለ የከፈተውን ካምፓስ እንዲዘጋ ተገዷል። እንዲሁም ሀያት፣ ቤቴል፣ አፍሪካ የጤና ሳይንስና አትላስ ኮሌጆች ከመስከረም ወር 2008 ዓ.ም ጀምሮ በዶክተር ኦፍ ሜዲሲን አዲስ ተማሪዎች መቀበል እንደማይችሉም ኤጀንሲው ይፋ አድርጓል፡፡

ሐራምቤ ኮሌጅም ከህግ ውጭ የመዘገባቸው ተማሪዎችን እንዲያሰናብትና የፈጸማቸውን የህግ ጥሰቶች እስኪያስተካክል ድረስ በመደበኛም ሆነ በርቀት መርሐ ግብር አዲስ ተማሪዎች መቀበል እንደሌለበት ኤጀንሲው አስጠንቅቋል።

በተመሳሳይ ሚሽከን ኮሌጅ

ከዚህ ቀደም ከመስፈርት ውጪ የመዘገባቸውን ተማሪዎች እንዲያሰናብት ተጠይቆ ተግባራዊ ባለማድረጉ በመማር ላይ የሚገኙትን ህጋዊ ተማሪዎች አስጨርሶ ፕሮግራሞቹን እንዲዘጋ ውሳኔ ተላልፎበታል።

በተመሳሳይ ሮያል ኮሌጅ፣ አንድነት ኢንተርናሽናል ኮሌጅና ዌስተርን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የማይገባቸውን የደረጃ ስያሜ በመጠቀማቸው ማስጠንቀቂያ ተላልፎባቸዋል።

እርምጃው በትምህርት ስርዓቱ የሚደርሰውን አደጋ በመቀልበስ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ያለመ ነው ተብሏል።

ትምህርት ላይ እያሉ ትምህርታቸው ለተቋረጠባቸው ተማሪዎች፣ መንግሥት ኮሌጆቹ ያስያዙትን የኢንሹራንስ ቦንድ በመጠቀም ቀሪ ትምህርታቸውን የሚጨርሱበት መንገድ ይመቻቻል ማለቱ ተዘግቧል። ዝርዝሩ ግን አልተገለጸም።

በአገር አቀፍ ደረጃ 96 ከፍተኛ የግል የትምህርት ተቋማት በማስተማር ላይ ይገኛሉ።

በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር አምባሳደር ግሬግ ዶሪ በአፍሪካ ኅብረትና በተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ቋሚ ተወካይም ናቸው፡፡ በቅርቡ የተካሄደውን ጠቅላላ ምርጫ፣ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ መያዝና የእስር ሁኔታ፣ በኢትዮጵያ ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከሪፖርተር ጋዜጣ ጋር ቃለ መጠይቅ አድርገዋል። በዚሁ ቃለምልልሳቸው ከሰጧቸው መልሶች የሚከተሉትን ቀንጭበናል።

“ይኼ እንደ ሰሜን ኮሪያ ባሉ አገሮች የሚከሰት ነገር ነው”

አምባሳደር ግሬግ የአውሮፓ ኅብረት ምርጫ 2007ን እንዲታዘብ አለመጋበዙን ገልጸው “ምርጫውን መታዘብ አለመቻላችን አሳዛኝ ነው፡፡” ነው ብለዋል። “መንግሥት የአውሮፓ ኅብረት ምርጫውን እንዳይታዘብ እንደሚፈልግ በግልጽ አሳይቷል፡፡ ባልተለመደ ሁኔታ ዲፕሎማቶችም ምርጫውን እንዳይታዘቡ ተከልክለዋል፡፡”

ከምርጫው አስቀድሞ በነበረው የፖለቲካ ምኅዳር መጣበብ ላይም ሥጋት ነበረን፡፡ አሁን ገዥው ፓርቲና አጋሮቹ መቶ በመቶ ፓርላማውን እንደሚቆጣጠሩ እየተሰማን ነው፡፡ በእኔ አስተያየት ይኼ ለዴሞክራሲ ጥሩ ነገር አይደለም፡፡ ይኼ እንደ ሰሜን ኮሪያ ባሉ አገሮች የሚከሰት ነገር ነው፡፡ በኢትዮጵያ ፓርላማ የተለያዩ አመለካከቶች ቢንሸራሸሩ ጥሩ ነበር፡፡ ባለፈው ፓርላማም ቢሆን ከ547 ወንበሮች ተቃዋሚዎች የተወከሉት በአንድ ግለሰብ ብቻ መሆኑ በቂ አይደለም፡፡ ወደፊት ፓርላማው ብዛት ያላቸውን የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ቢያቅፍ ኢትዮጵያ እያደገችና የዓለም አቀፍ ዴሞክራሲያዊ ማኅበረሰብ አባል ለመሆኗ ምልክት ይሆናል፡፡

“ተቃዋሚ ፓርቲዎች የተከፋፈሉ መሆናቸውንም ተመልክቻለሁ”

ስለተቃዋሚዎችም አስተያየታቸውን የገለጹት አምባሳደር ግሬግ “ተቃዋሚ ፓርቲዎች የተከፋፈሉ መሆናቸውንም ተመልክቻለሁ፡፡” ብለዋል። “ስለዚህ በቀጣይ ዓመታት ጉዳዩን እንደገና ሊመለከቱትና አብረው መሥራታቸው ውጤቱን የሚያሻሽለው ከሆነ ሊያስቡበት ይገባል፡፡ ፓርቲዎች በበዙ ቁጥር የመራጮችን ድምፅ ስለሚቀራመቱ የተሻለ ውጤት የማግኘት ዕድላቸውን ያጠባል፡፡ በማለትም መክረዋል።

አንዳርጋቸው ጽጌ “በተገቢው ሁኔታ ስለመያዛቸው ለማረጋገጥ አልቻልንም”

“በመጀመሪያ በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይ ላይ ለመናገር በጣም የተገደብኩ መሆኔን ለመግለጽ እወዳለሁ፡፡” ያሉት አምባሳደሩ የሚከተለውን ተናግረዋል፦ “ለአቶ አንዳርጋቸው ዲፕሎማሲያዊ

ዕርዳታ እያደረግን ሲሆን፣ ከቤተሰባቸውም ጋር ቅርብ ግንኙነት አለን፡፡ በዲፕሎማሲያዊ ዕርዳታችን ላይ ስላሉ ዝርዝር ጉዳዮች አስተያየት መስጠት አልፈልግም፡፡ ምክንያቱም ለቤተሰቡ ያልተገለጸን ነገር ለሌላ አካል መናገር ስለማያስፈልግ ነው፡፡ አቶ አንዳርጋቸው ከተያዙ በኋላ ሦስት ጊዜ አይቻቸዋለሁ፡፡ ከዚህ ውጭ ምን ማለት እችላለሁ? በተገቢው ሁኔታ ስለመያዛቸው ለማረጋገጥ አልቻልንም፡፡ የዲፕሎማሲያዊ ጉብኝቱ ዋነኛ ዓላማም ይኼው ነው፡፡ ኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን የሚገዛውን የቪየና ዓለም አቀፍ ስምምነት ፈራሚ አይደለችም፡፡ ለምን እንዳልፈረመች ባይገባኝም አንድ ቀን ፈራሚ እንደምትሆን ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ይሁንና የዓለም

አቀፍ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳን ፈራሚ በመሆኗ፣ የእስረኞች አያያዝን በተመለከተ ዓለም አቀፍ ደረጃ የማሟላት ግዴታ አለባት፡፡

አንድ የእንግሊዝ ዜጋ ውጭ አገር ሲታሰር ሥጋቶችና ልዩ ግዴታዎች አሉብን፡፡ የእንግሊዝ ሕዝብ እነዚህ ዜጎች በአግባቡና ዓለም አቀፍ መሥፈርቱን በጠበቀ መንገድ መያዛቸውን እንድናረጋግጥ ይጠብቃል፡፡ ከዚህ ውጪ በአጠቃላይ በሰብዓዊ መብት ላይ ሥጋት አለኝ፡፡ የሰብዓዊ መብት ምክር ቤትን ጨምሮ በተለያዩ ዓለም አቀፍ አካላት እንቅስቃሴ ላይ እንሳተፋለን፡፡ ስለዚህ በሌላ አገር ዜጎች የእስር አያያዝ ላይ ችግር ካለ እሱም ቢሆን ያሠጋናል፡፡ ሥጋቶቻችን የምንገልጸው መሠረታዊ መሥፈርቶች እንዳልተሟሉ ስናስብ ነው፡፡

ለአቶ አንዳርጋቸው እነዚህ መሠረታዊ መሥፈርቶች እንደተሟሉላቸው መናገር ይቻላል? በተገቢው ሁኔታ እንክብካቤ እየተደረገላቸው ነው?” የሚል ጥያቄ የተሰነዘረላቸው አምባሰደር ግሬግ “በዚህ ጉዳይ ላይ ለመናገር ገደብ ስላለብኝ አስተያየት ለመስጠት ፈቃደኛ አይደለሁም፡፡” ብለዋል። ሪፖተር የሚከተለውን ሌላ ጥያቄ አቀረበላቸው?

ሪፖርተር፡- አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች እንግሊዝ ለዜጋዋ ያልታገለችው አቶ አንዳርጋቸው በነበራቸው የፖለቲካ ተሳትፎ የተነሳ አማራጭ ስላልነበራት ነው ይላሉ፡፡ የአቶ አንዳርጋቸው የፖለቲካ እንቅስቃሴ ምን ዓይነት ተፅዕኖ ፈጥሮባችኋል?

አምባሳደር ግሬግ ዶሪ፡- በአጠቃላይ አቶ አንዳርጋቸው በኢትዮጵያ ከመያዛቸው በፊት ምን እየሠሩ እንደነበር አስተያየት መስጠት አልፈልግም፡፡ ምክንያቱም ይኼ ጉዳይ ወደ ችሎት ሊያመራ ስለሚችል ነው፡፡ ነገር ግን ዲፕሎማሲያዊ ጉብኝት አቶ አንዳርጋቸው ይሠሩ ከነበረው ነገር ጋር ግንኙነት የለውም፡፡ ምንም አደረጉ ምንም ዲፕሎማሲያዊ አገልግሎት አይነፈጉም፡፡

እንግሊዝ ግንቦት ሰባትን በሽብርተኝነት አልፈረጀችም

ሪፖርተር፡- በቅርቡ አሜሪካ በኢትዮጵያ ፓርላማ በሽብርተኝነት የተፈረጁ ቡድኖችን እንደምትቃወም በአደባባይ ገልጻለች፡፡ ከእነዚህ አንዱ አቶ አንዳርጋቸው አባል የነበሩበት ግንቦት ሰባት ነው፡፡ በእነዚህ ድርጅቶች ላይ የእንግሊዝ አቋም ምንድን ነው?

አምባሳደር ግሬግ ዶሪ፡- አባባሉን በትክክል ስለማየቴ እርግጠኛ አይደለሁም….

ሪፖርተር፡- ይኼንን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትር ዊንዲ ሼርማን በቅርቡ ከሰጡት መግለጫ መረዳት ይቻላል ብዬ ነው…

አምባሳደር ግሬግ ዶሪ፡- ዊንዲ ሼርማን አሜሪካ ግንቦት ሰባትን አትደግፍም ነው ያሉት፡፡ ይኼን እኔም አረጋግጥልሃለሁ፡፡ ግንቦት ሰባትንም ሆነ መሰል ቡድኖችን እንግሊዝ አትደግፍም፡፡ ነገር ግን እንግሊዝ ግንቦት ሰባትን በሽብርተኝነት አልፈረጀችም፡፡ ምክንያቱም በእንግሊዝ ዓውድ አንድን ቡድን ሽብርተኛ ብሎ ለመፈረጅ የሚያስችል ማስረጃ አላየንም፡፡ ቢሆንም ሕጋዊ መንግሥትን ለመገርሰስ የሚሠራ ማንኛውንም ቡድን አንደግፍም፡፡ የዊንዲ ሼርማን መግለጫ በተለያዩ ሚዲያዎች በትክክል እንዳልተንፀባረቀ ግን እረዳለሁ፡፡ በትክክል ምን እንዳሉ አላውቅም፡፡ በጉዳዩ ላይ አሜሪካ ያላት ፖሊሲ ግን ከእንግሊዝ ፖሊሲ መሠረታዊ ልዩነት እንደሌለው ግን አምናለሁ፡፡

ስለ ምርጫው-

“ይኼ እንደ ሰሜን ኮሪያ ባሉ አገሮች የሚከሰት ነገር ነው”

ስተለቃዋሚዎች ፓርቲዎች -

“የተከፋፈሉ መሆናቸውንም ተመልክቻለሁ”

ስለ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ -

“በተገቢው ሁኔታ ስለመያዛቸው ለማረጋገጥ አልቻልንም”

ስለ ግንቦት ሰባት-

“እንግሊዝ ግንቦት ሰባትን በሽብርተኝነት አልፈረጀችም!”

በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር አምባሳደር ግሬግ ዶሪ ምስክርነት

I believe she ( Windy Sherman, undersecretary of US State department) said that the US does not support Ginbot 7 and I can say the same thing. Of course, we do not support Ginbot 7 or groups like it. And neither has Ginbot 7 been proscribed

as a terrorist group in the UK; because we have not seen the evidence that would be considered suitable in a British environment to proscribe the group. But, we don’t

support any group that seeks the overthrow of a legitimate government. I know that Wendy Sherman’s statement was not always reflected accurately in the media. So, to be honest, I don’t know exactly what she said but I do not believe that the position

of the US government is in substance any different from that of the UK government. British Ambassador to Ethiopia,Ambassador Greg Dorey

እንደቀልድ!በንግግራችን መካከል ስልክ ሲቋረጥ ምነው ባክህ በኢትዮጵያ መብራት ነው እንዴ ስልክህ የሚሠራው አለኝ። ሁሌ እንደቀለደ ነው።

አንዱ እነዚህ ሰዎች ሥራ ይሠራሉ ሌላው ግን ዝምብሎ ወሬና ሐሜት ብቻ ነው ብሎ ሲተች ሰማውና። አዎ እሱስ እውነት ብለሃል ሁሉንም ነገር ለብቻቸው እየሠሩ ለሐሜትና ለወሬ የሚበቃ ጊዜ ከየት ያመጣሉ ብለህ ነው ታዲያ? ብሎ መለሰለት።

አንድ ጊዜ ደግሞ የምርጫውን ውጤት የሰማ ሰሞን፣ ኤርምያስ ለገሠን አግኝቶ እንደዚህ አለው። "ስማ እንጂ አንተ ኤምርያስ እነዚህ የወያኔ ሰዎችን በተለይም ጀኔራሎችን አልተማሩም 5ኛ ክፍል አልጨረሱም እያልክ ተናግረህ ተናግረህ ይኸው አሁን በእልህ ተነስተው ምርጫውን መቶ በመቶ ደፈኑልህ አይደል!" ብሎ ቀለደ።

አየርላንድ ላይ ከኢትዮጵያ አየርመንገድ ወርደው እጃቸው ስለሰጡት ሰዎች ምን አስተያየት እንዳለው ሲጠየቅ አያይ ምን ይኖረኛል። ያው ሰባት መሆናቸው የተሰማ ቀን ግንቦት ሰባት ናቸው እንደሚሏቸው ከመገመት ውጭ ምን ይባላል? ለነገሩ አሁን ስምንት ስለተባለ ተርፈዋል። ብሎ መለሰ።

ይሄስ ሼህ አል አሙዲ ከልጅቱ ጋር ያደረጉት ነገር እውነት ይመስላሃል ወይስ ወሬ ነው ተብሎ ተጠየቀ። ነገሩስ የቆየ ነው። ግን ይቅርብኝ ፖለቲካ አታናግረኝ። ይልቅ ልጅቱ ጎበዝ የፊልም ተዋናይ ሆና ዲቪዲዋን እየቸበቸበች መኖር ስትችል፣ "ለምን እንዲህ አደረግሽ ? " ተብላ ስትጠየቅ የሰጠችው መልስ ነው ደስ ያለኝ።

ምን አለች?

ከሺ ዲቪዲ አንድ አል አሙዲ!

ፎቶ ሪፖርተር

ለአባይ ቦንድ እስካሁን ከዳያስፖራው የተገኘው 30 ሚሊዮን ዶላር ነውከአሜሪካ 5.6 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ነውዳያስፖራው ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 30ሚሊዮን ዶላር ወይም 600ሚሊዮን ብር ቦንድ መግዛቱን የግድቡ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት አስታወቀ።

ለግድቡ ግንባታ እስካሁን ዳያስፖራውና ሕዝቡ ያዋጡት 7 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር እንደሆነም

ተነግሯል።

የጽህፈት ቤቱ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኃላፊ አቶ ፈቃዱ ከተማ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት፥ ከዳያስፖራው በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ ቦንድ በመግዛት ቀዳሚውን ስፍራ ይዘዋል።

አፍሪካ ውስጥ የሚኖሩ ዜጎች ደግሞ 5.65ሚሊዮን ዶላር ወይም የ113 ሚሊዮን ብር ቦንድ በመግዛት በሁለተኛነት ደረጃ ላይ ይገኛሉ።

በአሜሪካ የሚኖሩ 5.6 ሚሊዮን ዶላር ወይም 112 ሚሊዮን ብር ቦንድ በመግዛት ለግድቡ እውን መሆን አስተዋጽኦቸውን ማበርከታቸውንም ተናግረዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን በኦሮምኛ ቋንቋ መጽሔት ማሳተም ጀመረ

በማኅበረ ቅዱሳን የኅትመትና ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ዋና ክፍል በኦሮምኛ ሚዲያ ፕሮጀክቱ ተቀርጾ ለኅትመት የበቃው Dhanga Lubuu/ የነፍስ ስንቅ/ የተሰኘ መጽሔት ሰኔ 14 ቀን 2007 ዓ.ም. በማኅበሩ ሕንፃ መሰብሰቢያ አዳራሽ ማስመረቁን አስታወቀ።

ማህበሩ በድህረ ገጹ ላይ ባወጣው ዜና “ለምረቃ የበቃው መጽሔት የታተመበት ዋና ዓላማም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያትን ሂዱና ዓለምን ሁሉ አስተምሩ /ማቴ.28፡19/ ባለው አምላካዊ ቃል መሠረት የአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ኦሮምኛ ለሆኑ ምእመናን የቤተ ክርስቲያንን ትምህርተ ሃይማኖት፤ ሥርዓተ እምነትና ትውፊት በቋንቋቸው እንዲረዱ ማስቻል እንደሆነ በምረቃው ወቅት” መገለጹን ጽፏል።

መጽሔቱ ትምህርተ ሃይማኖት፤ ስብከት፤ ቤተ ክርስቲያናችን፤ ነጽሮት እና ሰሞነኛ የተሰኙ ርዕሰ ጉዳዮችን የሚዳስሱ ዓምዶችን መያዙም ተገልጿል።

በርካታ ምእመናን ተገኝተውበታል በተባለው የምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ በኦሮምኛ ቋንቋ የወንጌል ትምህርትና ያሬዳዊ ዝማሬ መቅረቡ ተገልጿል።

ከዚህ በፊት ለአገልግሎት የበቃው የኦሮምኛ ድረ ገጽ /eotcmk.org/afaanoromo/ የዚሁ የኦሮምኛ ሚዲያ የፕሮጀክት አካል መሆኑንም የማህበረ ቅዱሳኑ ድህረ ገጽ ዘግቧል፡፡

መንግሥት በኢትዮያ የጤና ኢንሹራንስ እጀምራለሁ አለመንግሥት የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድን አገልግሎት በመላው ሃገሪቱ እንደሚጀምር የኢትዮጵያ ጤና መድን ኤጀንሲ አስታወቀ።

አገልግሎቱ ከ2003 ዓ ም ጀምሮ በአማራ ፣ ትግራይ፣ ኦሮሚያና ደቡብ ክልሎች በ198 ወረዳዎች በተደረገው ሙከራ ውጤታማ በመሆኑ በመላ ሃገሪቱ ተግባራዊ ለማድረግ መነሳቱን አስታውቋል።

በሙከራውም 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን የሚደርሱ አባራዋራዎች የጤና መድን አባል የሆኑ ሲሆን፥ የአባላቱን ቤተሰቦች ጨምሮ ከ5 ነጥብ 6 ሚሊዮን የሚበልጡ ሰዎች ተጠቃሚ ማድረግ እንደተታችለው ገልጿል።

ይህንን ለማሰፈጸም የሚረዱ 24 ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች እና ተጨማሪ 20 ቅርንጫፎች ዝግጁ ሆነዋል ።

Page 5: Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 … 92.pdf · Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, ... በቀድሞው

5

ርዕሰ አንቀጽዘኢትዮጵያ ጋዜጣ በሰሜን አሜሪካ በተለይም ዋሽንግተን ሜሪላንድና ቨርጂኒያ ነዋሪ ለሆኑ ኢትዮጵያውያን ከጁላይ

2002 ጀምሮ የሚታተም፣

202 518 0245 P.o.box 2049,

Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com

[email protected] Newspaper Editor - Dereje Desta አዘጋጅ ደረጀ ደስታ

ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ Zethiopia Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com

ፕሬዚዳንት ኦባማ ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው። ምን ይመለከቱ ይሆን? ኢትዮጵያ ምን መስላ ትታያቸው ይሆን? በዓይነ ሕሊናቸው የሳሏት ኢትዮጵያ ካለች ከሱ ጋር ያጣጥሙት ይሆናል። ያው እንደሚጠበቀው “ውብ አገር ነው ያላችሁ ” ማለታቸው አይቀርም። አስተያያታቸውን ውበት እንደተመልካቹ ነው ብለን አናጣጥለውም። ይልቁንም እኛ ከምናውቃት ኢትዮጵያ ጋር እናስተያየዋለን። በአገር ያለንም የሌለንም ኢትዮጵያውያን የዛሬዪቷን ኢትዮጵያ በዓይነ ሕሊናችን ስለን የምንመለከተው እንዴት አድርገን ይሆን?

ኢትዮጵያ ባንኖርም እዚህም እዚያም በመዶሻ የሚቀወረው ሚስማር ጩኸት ይሰማናል። ኢትዮጵያ ፈርሳ እየተገነባች ወይም እንደ ቡቱቶ ድሪቶ ተቀዳ እየተደረተች፣ በሙቅ እየተለበደች፣ በቅብ እየተሸነገለች መሆኑ ይታየናል። ኢትዮጵያ ሸቀጥ እየተራገፈባት፣ ገበያ እየደራባት፣ ለውጭ ፀሐይ የተጋለጠው ባህሏ ቀልጦ እየፈሰሰባት፣ ልጆችዋን አስርባ ባዕድ እያጠገበች መሆኑ ይታየናል። ምድሯ ተቀርድዶ፣ ገመናዋ ተበርግዶ፣ ወርቋ እየተዛቀ፣ ጥሪቷ አልቆ ወዟ እየተጨመቀ መሆኑም ይታየናል። ዉበት እንደተመልካቹ ነው።

አያይ እንደሱ አይደለም። ኢትዮጵያ በተሐድሶ እየታደሰች፣ ወደ ጥንት ገናናነቷ እየተመለሰች ነው። ወንዟቿን እየገደበች፣ መንገዶቿን እያነጠፈች፣ የባቡር መስመር እየዘረጋች፣ ስሟን ከረሀብ ወደ ጥጋብ ለመለወጥ፣ ኢኮኖሚዋን እያስፈነጠረች ነው። ኢትዮጵያ ሰማይን በህንጻዎችዋ እየጠቀሰች፣ የአፍሪካ መዲናነቷን እያጸናች፣ ዲፕሎማሲያዊና ወታደራዊ ጉልበቷን እያፈረጠመች፣ የገናና አገር መሪዎች ሁሉ ሊጎበኝዋት የሚጣደፉባት አገር ሆናለች። ውበት እንደተመልካቹ ነው።

አያይ እንደሱ አይደለም። ኢትዮጵያ ልጅችዋ አገር እየለቀቁ፣ ከባህር እየጠለቁ፣ ከህንጻ እየወደቁ፣ በገመድ እየታነቁ፣ በካራ እየተሰነጠቁ ደማቸው እስከነ እድሜያቸው የትም እየፈሰሰ ነው። ኢትዮጵያውያን ለአረመኔዎቹ ግርድና፣ ለአውሬዎቹ እሽክርና ተሸጠዋል። ኢትዮጵያውያን ህጻናት፣ በጉዲፈቻ ስም፣ እንደ ኤክስፖርት እቃ እየተቀረቀቡ፣ የደላላ ሲሳይ ሆነዋል። ኢትዮጵያውያን ከምድር ቀያቸው እየተፈናቀሉ፣ ከርስታቸው እየተነቀሉ፣ መሬታቸው የህንድና የቻይና ወሮበላ ነጋዴዎች መጫወቻ ሆኗል። ውበት እንደተመልካቹ ነው።

አያይ እንደሱ አይደለም። ኢትዮጵያውያን አርሶ አደሮች ዛሬ ሀብታም እየሆኑ ነው። መንገድ ገብቶላቸዋል ፤ ውሃ ተቆፍሮላቸዋል ፤ ክሊኒክ በየመንደሩ አለ። ትምህርት ቤቶች እስከ ዩኒቨርስቲዎች እንደ አሸን እየፈሉ ነው። ፋብሪካዎች እዚህም እዚያም ናቸው። በርካታ ሚሊየነሮች ተፈጥረዋል፤ በየከተሞች የኮንደሚኒየሞችና የመኖሪያ ቪላዎች፣ በብዙ ሺዎች እየተሠሩ ነው፤ በርካታ ሰዎች የኮንስትራክሽን ስራዎች እያገኙ ነው፤ ዘመናዊ ሆቴሎች እየተስፋፉ ነው። እነዚህ ሁሉ ሐሰት አይደሉም፤ የሚታዩ፣ የሚነኩ፣ የሚለኩ ናቸው። ውበት እንደተመልካቹ ነው።

አያይ እንደሱ አይደለም። እድገቱ ቢወደድም ኑሮም አብሮ ተወዷል። ኢኮኖሚ ወደላይ ሰዎች ወደታች እያደጉ ነው። በዚያ ላይ እስር ቤቶች በሰዎች ተሞልተዋል። ፍርሃት ነግሷል፤ ፍትህ ጠፍቷል። ፍርድ ቤቶች መቀለጃ እየሆኑ ነው። ሙስና በዝቷል። ሀሳብን በነጻነት መግለጽ አይታሰብም። በዚህ ዘመን ይሉኝታ ያጣ፣ አይኑን ያፈጠጠ፣ የመቶ በመቶ አሸነፍኩ ምርጫ እየተካሄደ ነው። የአንድ መንደርና ክፍለ አገር ልጆች ብቻ ተለይተውና ታምነው ለሁነኛው ቦታ እየተሾሙ፣ ከአጫፋሪዎቻቸው ጋር አላግባብ እየበለጸጉ ጠግበው እየባለጉ ነው። ሰዎች በጎጥ ማንነት ተከፋፍለው እየተባሉ ሊገዳደሉ ቀንና አጋጣሚ እየጠበቁ ፣ ቂም እየጠመቁ፣ ለበቀል እያሸመቁ መሆኑ ግልጽ ነው። በኢትዮጵያ ጥላቻ ነግሷል ፤ ጥርስ ተነክሷል። ሆኖሎት መቦጨቅ የጀመረ ቀን አገር ይዘለዘላል። ይህን አደጋ በቅራቅንቦ ደልለው አያስጥሉትም። የሊቢያ ብልጽግና ሊቢያን አልታደጋትም። መጪው ጨለማ ነው። ከትላንቱ ይልቅ ነገው ያስፈራል። ውበት እንደተመልካቹ ነው።

አያይ እንደሱ አይደለም። ዓለም እየመሰከረ እድገቷን እየተናገረ ነው። ኢትዮጵያ የእድገት ተምሳሌት ሆናለች። አጀንዳዋ ሁሉ ልማት ነው። በለውጥ ጎዳና እየተራመደች ህዝቧን በአጭር ጊዜ ውስጥ መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገሮች ተርታ ለማሰለፍ አልማ እየሠራች ነው። በየአምስት ዓመቱ የልማት የእድገትና የትራንስፎርሜሽን ራዕይ አውጥታ እሱን በተግባር ለማዋል ሌት ተቀን እየሠራች ያለች አገር ናት። የተሰራው ነገር ሁሉ የማይጥማቸው ፣ ወርቁ ፋንዲያ የሚሆንባቸው፣ በጥላቻ የታወሩ፣ ጊዜ ያለፈባቸው፣ ትናንትን ናፋቂዎች ሁሌም ተቃዋሚ ናቸው። የነሱን አስተያየት ለመቀየር ምንም የሚደረግ ነገር የለም። ውበት እንደተመልካቹ ነው።

አዎ እንግዲህ ውበት እንደተመልካቹ ነው። አስተያየትም እንደሰጪው ትችትም እንደተቺው ነው። ግን አንዳንድ ተመልካች ውበትን ሲመለከት በአንድ ዓይኑ አይደለም። አንዱን አብርቶ አንዱን አጥፍቶ አይመለከትም። ሁለቱንም ያያል። ለነገሩ የማንም ዓይን ቢሆን መርጦ አይመለከትም። ስለተመለከተው ነገር የሚሰጠው አስተያየት የተለያየ ይሆናል እንጂ መሬት ላይ ያለውን እንዳለው አድርጎ ይመለከተዋል። የዛሬዪቱ ኢትዮጵያ ከተገለጠ ዓይን አልተሰወረችም። ውበቷም ጥፉነቷም ቁልጭ ያለ ነው። ተምረው ሥራ ያጡ፣ መሯቸው ከአገር የወጡ፣ ግራ ገብቷቸው በድህነት ተኮራምተው የተቀመጡ፣ በእስርና በሞት የተቀጡ ሰዎች በሙሉ ምንም ነገር ማየትና ማስተዋል አያስፈልጋቸውም። እነሱ ራሳቸው ይታያሉ እንጂ እንዲያዩ አይጠበቅባቸውም። እነሱ ራሳቸውን ማስረጃ አድርገው ከራስ በላይ ነፋስ ብለው ኢትዮጵያን አጨልመው ቢመለከቱ፣ ውበት እንደተመልካቹ ነው ተብለው ሊተቹ አይችሉም። ለነሱ ፖለቲካ ሕይወት እንጂ አስተያየት አይደለም። ኢትዮጵያ ላይ የሚብለጨለጨው ነገር በሙሉ እነሱን ያልተመለከተ፣ እነሱን ያገለለ ነውና እንኳን በጎ ሊናገሩ ጨርሶ ቢጠሉት አይገርምም።

በሌላ በኩል ደግሞ ቀን የወጣላቸው፣ እውቀት ሳይሆን ማንነት ብሔር እንጀራ የሆናቸው፣ መወለድ መዛመድ ፕሮፌሽን ሆኗቸው፣ ማጭበርበር ቀንቷቸው ጌታ ሚሊየነር፣ የቅርብ ሰው የእልፍኝ አሽከር ሆነው፣ “ኢትዮጵያ ገነት ናት!” ቢሉ ውበት እንደተመልካቹ ነው ተብለው አይተቹም። እነሱ ራሳቸው በትዝብት ይታያሉ እንጂ ለማየት አልተጠሩም። ስለሆነም ምንትስ በበላበት ይጮኻል ተብሎ ዝም ይባላል እንጂ እነሱን ከቁምነገር ቆጥሮ የሚሰማቸው አይገኝም። መቸም ውበት እንደ ተመልካቹ ሳይሆን እንደ በላተኛው ነው ተብሎ አዲስ ተረት አይወጣላቸውም። ቢሆንም ቢሆንም ሆዳም ሰው ይኸው ፎቅ ተሠርቷል ብሎ መሰክሯልና ፎቁ የለም መንገዱ አልተሰራም ማለት አይቻልም። የሆዳምን ለሆዱ የፎቁን ለፎቁ መስጠት ይገባል። እውነት በማንም ስለተነገረች አትከሽፍም። ልማትም ለልማት ዘረኝነትም ለዘረኝነት ይሰጣል። መሥራቱን ሠርቷል ግን ዘረኛ ነው ማለት የግድ ነው። አገሩን ይወዳል ግን ምንም ነገር ሠርቶ አያውቅም በማለት የጨበጣ አርበኝነትም መገሰጽ ያስፈልግ ይሆናል። የቁርጥ ቀን ልጅነት እንዲህ ጥንቡን ጥሎ ማንም እየተነሳ በየፌስቡኩ ሲሸነጋገልበት እንደሚወለው ጨዋታ ማድረግም ተገቢ አይደለም። ወስላቶቻችንን በነፋስ ላይ እንዲያወሩ ብቻ ሳይሆን የተጨበጠ ነገር እንዲሰሩም መምከርም ተገቢ ነው። ካልሆነ ግን ዛሬ እንዲወድቅ የፈለግነው ሥርዓት አንድም ቶሎ አይወድቅም። ውሎ አድሮም ቢሆን ግን መውደቁ አይቀርም። ያኔ ማጣፊያው ያጥረናል። 60 ቦታ የተፈነካከተው የተቃዋሚ ጎራ ችግርም አንዱ ይኽ እርስ በርሱ መፈራረጁም ጭምር ነው።

ስለሆነም ይህን ሁሉ ግራና ቀኝ አይቶ፣ ጥፋትና እንከንን ተመልክቶ፣ አንተም አንተም ብትሆኑ ብትሰሙ ይሻላችኋል ማለት የሚችል የበቃ ሰው ያስፈልጋል። ለነገሩማ ፍርድ ቤት እንኳ ለበቃ ምስክርነት፣ ለሚዛን ለዳኝነት የሚበቃን ሰው ለማጨት “ ጠብ ዝምድና አላችሁ?” ብሎ ይጠይቃል። በኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዳይም ላይ ለመነጋገር ጠብ ዝምድና የሌላቸው አስተያየት ሰጪዎች ቢኖሩ አገርና ነገር ይቀኑ ይሆን ብሎ መመኘት ይቻላል። ምክንያቱም ተናግሮ የሚደመጥ፣ አስተያየት ዳኝነቱ የሚመረጥ ሰው እየጠፋ መሆኑ የሚታይ ይመስላል። እርግጥ ነው ፖለቲካ የሚቀናው ተበዳዮች ተነስተው ሲያምጹ ነው። አገር ግን በአመጽ ብቻ አልቀና ብሏል። ምክንያቱም ወይ አመጹ አልመጣም ወይም እየመጣ የሄደው አመጽ ጥሩ ትምህርት ትቶ አላለፈም። ምን በቀደደው ምን ይገባል። በየአገሩ የሚያዩት አመጽም የሚመኙት አልሆነም። ታዲያ ምን ይሻላል ቢባል ያው እነዚያኑ ገላጋዮች ፈልጎ ማግኘት ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ እንደሆነ ያልተነካ ግልግል ያውቃል ብሎ ገላጋዮችን ቢያሽሟጥጥም በገላጋይ የማመን ሽምግልናን የማክበር ባህል አለው። ለዚያ ሽምግልና የሚበቁ ራሳቸውን ከስሜታዊነት ያረቁ ሁለቱንም ሶስቱንም ሁሉንም ወገን በእኩል ዓይን ሊያዩ የሚችሉ ኢትዮጵያውያን ያስፈልጉናል። ቁምነገሩ ከውበቱ ሳይሆን ከተመልካቹ መሆኑ ካልቀረ ውበት እንደተመልካቹ ነው ለሚለው ተረታችን ውብ ተመልካች ያስፈልገናል። ሽምግልናኮ የግድ ግራና ቀኝ ማስቀመጥ አያስፈልገውም። ቅን አስተያየት አቀራራቢ አስታራቂ ስብከት ወጣ ያለ የበሰለ አንደበት በራሱ ሽምግልና ነው።

ካልሆነ ግን በእንዲህ ያለ ዓይን ያወጣ የዱርዬ ምርጫ ሥርዓት እንዴት ልንገፋው ነው? በእንዲህ ያለ የርስ በርስ ጥላቻ እንዴት ልንዘልቀው ነው? ምኑንም ከምኑ የማያውቁ ገና አድገው ያልበቁ ህጻናትና ኮረዶችን በፖለቲካና ሽብርተኝነት አስረን እያንገላታን፣ አንዱን ዘር ሌላው ዘር ላይ እያስነሳን ሌላውን በሌላው ላይ ጥርስ እያስነከስን እንዴት እንገፋዋለን? ሰው ሁሉ በአገሩ ተንቆ - አገሩን ንቆ እየተሰደደ፣ እድገትን መስበክ እንዴት ይቻለናል? ኢትዮጵያውያን ተደስተውና ኮርተው የማይኖሩባት ኢትዮጵያ የምትገነባው ለማን ነው? ድምጥማጧ ይጥፋ የሚባለውስ ደግሞ ለማን ልትተርፍ ነው?

ከወዲህስ በኩል ደግሞ ያለነው ማንም ይሞገስበት ማንም፣ ይህን ሁሉ ጥሪት የጠጣውን የአባይን ግድብ ነገ ምን ልናደርገው ነው? ይህን ሁሉ የተዘረጋው መንገድ እናፈራርሰው ይሆን? ወይስ ያን ሁሉ እየፈላ ያለ ህንጻ በቡልዶዞር ልንሄድበት ነው? የባቡር ሐዲዱን እንነቅለው ይሆን? እንግዲያውስ ነገ የኛው ከሆነ የምንቃወመውን እየተቃወምን የሚበጀንን ለምን አንድገፍም? ምናልባት የኛ አይደለም ያልነው ነገር ሁሉ የኛ ካልሆነ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል እያልን ይሆን? ሚዛናዊነትኮ ነገሮቹን ሁሉ እኩል ማስቀመጥ አይደለም። ነገሮችን እንደሆኑት አድርጎ ለመናገር መድፈርም ጭምር ነው። 90ው ቢጎድል ስለ አስሪቷ በጎነት ማውራት ሚዛናዊነት ነው።

እስኪ ኑና ከሀሳብ እንላፋ፣ እስኪ ላለማረር እንገላበጥ? እስኪ በዚህ በዚህ እንኳ እደግፋለሁ ይህን ይህን ግን እቃወማለሁ የማለት ባህል ይኑረን? በግልባጩም ደግሞ እንዲሁ አባይን ገደበ ብለን ጭልጥ ብለን ስንደግፍ ሰዎችንም ደግሞ ያላግባብ ገደለ የማለት ብርታቱ ይኑረን። ልማቱ ለአፍታም ቢሆን መቋረጥ የለበትም፣ ውሎ አድሮ ለአገር ነው ለማለት የደፈርነውን ያህል፣ ዴሞክራሲም ሰብዓዊ መብትም መጣስ የለበትም፣ ኢትዮጵያዊ አንድነታችን በጎሰኝነት በሽታ መታወክ የለበትም ብለን ለመናገርም እንድፈር! እኛ እንኳ ድፍረቱ ቢያቅተን የሚፍጨረጨሩትን አንግደል። ስለዚህ በግራ ቀኙ ሆነን በአጓጉል የአቋም ጥራዝነጠቅነት ተቸክለን አቋም አቋም አቋም አንበል። አቋም ከቅንነት ጋር ነው ፤ አቋም ከተቻቻይነት፣ አቋም ከብልህነት ጋር ነው። ብልህነትም ከማሰብ፣ ማሰብም ከግራ መጋባት ይወለዳልና ግራ ይግባን! ይሄ ግብዝ ያደረገንን እርግጠኝነታችንን በጥርጣሬ እንፈትሸው። ያልጠረጠረ ተመነጠረ!

ስለሆነም ይህን የችግር ዘመን በብልሃት እንርታው። ችግሮቻችንን ሰማይ አድርሰን አናጋን። ደግሞግም በኛ ብቻ አልደረሰም። ዓለም ራሱ በብዙ እየተቸገረ፣ እየተሸበረ፣ ግራ በመጋባት እየተተራመሰ መሆኑን እያየን ነው። እሱንም ከግምት አስገብተን፣ ከተቸከልንበት ነቅነቅ ብለን አዟዙረን እንመልከት። ለምሳሌ አሁን ኦባማ ኢትዮጵያ ለመጎብኘት ሲሄዱ መጡልን ብሎ ከመፎከር እና ሄዱብን ብሎ ከማፈር ጫወታ የሚያድነን በትልቁ የተከፈተ ዓይን ሲኖረን ነው። መቸም የኦባማ ጉብኝት “ጠቅላይ ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ ባደረጉላቸው ግብዣ ነው” ተብሎ ሲነገር ከሚናደድና ከሚደሰት ትውልድ ያቺ አገር መፍትሔ ታፈልቃለች ተብሎ አይጠበቅም። ነገራችንን ሁሉ የድልና የውርደት አድርጎ ከመተርጎም የምንድነው ሁሉንም ነገር ከራሳችን ስሜት ጋር ብቻ አያይዘን ከመመልከት ስንድን ነው። አገርም ትድን ዘንድ አንዱ መንገድ እሱ ነው። የሚታየውን ክደን የማይታየውን አምነን አንዘልቀውም። ስለዚህና ስለሆነም ውበት እንደተመልካቹ ሳይሆን ውበት እንደ ውበትነቱ ይሁንልን።

ሰሞኑን የኢትዮጵያ የፌደሬሽን ምክር ቤት ለቅማንት ማህበረሰብ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሰጠውን የብሔረሰብነት እውቅና በማጽደቅ ብሔረሰቡ በፌደሬሽን ምክር ቤት ወንበር እንዲኖረው መወሰኑን የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘግቧል።

ከማህበረሰብነት ወደ ብሔረሰብነት የተሸጋገረው ቅማንት ከእንግዲህ የሚያነሳቸው አስተዳደራዊ ጉዳዮችም የክልሉ መንግስት በሰጠው ውሳኔ መሠረት እንዲቀጥሉ ምክር ቤቱ ውሳኔ መስጠቱም ተገልጿል።

እንደ ቅማንት ሁሉ የብሔረሰብነት ጥያቄ ያቀረበውና በደቡብ ክልል የሚገኘው የከንቱማ ማሕበረሰብ ግን ያቀረበው የብሔረሰብነት ጥያቄ ተቀባይነት አላገኘም። ማሕበረሰቡ የራሱ ቋንቋ የሌለው በመሆኑ ምክር ቤቱ ሳያጸድቀው ቀርቷል፡፡

ይልቁንም ማህበረሰቡ ጥያቄውን እንዲያነሳ ያስገደደው የመገለልና አስተዳደራዊ ችግሮች በመሆናቸው በክልሉ በየደረጃው ያሉ የአስተዳደር አካላትና ምክር ቤቶች በትኩረት ጉዳዩን እንዲፈቱ የፌደሬሽን ምክር ቤት ጽህፈት ቤትም ጉዳዩን እንዲከታተል ተወስኗል፡፡

በከፍተኛ ውዝግብ ውስጥ በሚገኙ የማህበረሰብ አባላትና አዳዲስ የብሔረሰብነትና ተያያዥ ጥያቄዎች እየቀረቡ ሲሆን የህገመንግሥት ጉዳዩችን እንዲተረጉምና እንዲቆለምም ከፍተኛ ሥልጣን የተሰጠው የፌደሬሽን ምክር ቤት፣ ከቋሚ ኮሚቴው 52 የህገ መንግስት ትርጉም ጥያቄዎች

የቀረበሉት ቢሆንም አምስቱን የተረጎመ ሲሆን 44ቱን ትርጉም የማያስፈልጋቸው ሲል ወስኖባቸዋል፡፡

የፌዴሬሽን ምክር ቤት በፌዴራሉ መንግሥት አባል ክልሎች የሚገኙ ብሔሮች፣ብሔረሰቦች፣ ሕዝቦች የሚልኩዋቸው አባላት የሚወከሉበት ምክር ቤት ነው፡፡ አንዳንዶች እንደ አሜሪካው ሴኔት ይመስሉታል። የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች፣ ሕዝቦች የራስን ዕድል በራስ የመወሰን እስከ መገንጠል መብትን በተመለከተ በሚነሱ ጥያቄዎች ላይ በሕገ መንግሥቱ መሰረት ይወሰናል፡፡

ቅማንቶች በአማራ ክልል ጎንደርና አካባቢዋ ነዋሪ ሲሆኑ የራሳቸውን ማንነትና ታሪክ እንዳላቸው የሚገልጹ ናቸው። ከዚያም አልፎ ስለጎንደርም ሆነ ስለ ነገሥታቱ ታሪክ ከኛ የበለጠ ሊያውቅ የሚችል የሚል መከራከሪያ ያነሳሉ። የሰሜን ኢትዮጵያንም የተፈጠረችው በቅማንት መሆኑን እየጠቀሱ ይከራከራሉ።ትግሬና አማራ ሁሉም ቅማንት ነው የሚሉትና የዚህ አሳብ ዋና አቀንቃኝ መሆናቸውን ከሚገልጹት ውስጥ አቶ ነጋ ጌጡ አንዱ ናቸው፡፡ በጁላይ 19/2014 ለወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ ሲናገሩ እንደዚህ ብለዋል

መጀመሪያ የቅማንትን የማንነት ጥያቄ ይዤ የተነሳሁት እኔ ነኝ የቅማንት ብሄረሰብ የልማት ማህበርን በ1984 መሰረትኩ። በዚያ ማህበር ስም እየዞርኩ “እኔ ቅማንት ነኝ” እያላችሁ ራሳችሁን ግለፁ፡፡ ህገ መንግስቱ ለኛ መጥቷል፤ ተጠቃሚ መሆን አለብን” እያልኩ ከሃገር ሃገር በእግሬ እየዞርኩ አስተማርኩ፡፡ እግረ መንገዴንም “የቅማንት

ህዝብ ታሪክ” የምትል ትንሽ መፅሐፍ ፃፍኩ፡፡ እሷ ከወጣች በኋላ በብሄረሰቡ ዙሪያ ውይይቱ ተስፋፋ፡፡ መፅሃፏ ትኩሳት አጫረች። በዚህ የተነሳ ብዙ መከራ ደርሶብኛል፡፡ የቋንቋው ት/ቤቶችን በየቀበሌው ቤት ተከራይተን በመክፈት ማስተማሩን ተያይዘነዋል፡፡ (የቋንቋ ተናጋሪነቱን መስፈርት ለማለፍ ማለት ነው።)

ጎንደር ቅማንት ነው የሚሉት አቶ ነጋ ትግሬውም ቢሆን ያው ነው ባይ ናቸው። ታሪኩን ከሳቸው አንጻር እንዲህ ያንበለብሉታል “ ትግሬ ማለት በቅማንትኛ “ሰው ሳይመጣ” ማለት ነው። ከዚያ ደግሞ እንደርታ ተባለ፤ “ሰው መጣ” ማለት ነው፡፡ “አጋመ” ቅማንትኛ ነው፤ “የኛ ያልሆነ” ማለት ነው፡፡ ግዕዝ ቋንቋን ተቀበል ሲባል “የኛ ያልሆነን አንቀበልም” ብሎ በመቃወሙ የተሰጠ ስያሜ ነው። “ይርትላ” ኤርትራ ነው፤ “ሰው አልመጣም” ማለት ነው፡፡ እነ ሙሴ ባህረ ኤርትራን ሲያቋርጡ፣ እነሱን የተከተሉት በባህር ውስጥ ሰጥመው ቀሩ፤ ዞረው ሲያዩ ሰው አልመጣምና በዚያው “ሰው አልመጣም” ብለው ሰየሙት፡፡ እንግዲህ ኤርትራም ሆነ ትግሬ ቅማንት ነው ማለት ነው፡፡

ይህ ታሪክ አሁን እውቅናም ወንበርም ተሰጥቶታል ። በኦሮሚያ ክልል ዝዋይ ሐይቅ ደሴት ላይ የሚኖሩት የዛይ ማኅበረሰብ የማንነትና ራስን የማስተዳደር ጥያቄ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አቅርበው ውይይት እየተደረገበት ካሉት አንዱ ሆኗል። ስለዚህ እንግዲህ አንድ ሰሞን ደግሞ አገር በዚህ ሊንጫጫ ነው ማለት ነው።

ቅማንት የብሔረሰብነት እውቅናና ወንበር ተሰጠውከንቱማ ግን በከንቱ ሆነ - ዛይ እየተጣራ ነው

የቻይና መስሎን ነው

በመገንባት ላይ ባለው የባቡር መስመር ዘረፋ እየተፈጸመበት ነውእስካሁን ከ100 ጊዜ በላይ ሙከራ ተደርጓልግንባታው በመገባደድ ላይ ባለው የአዲስ አበባ-ሜኤሶ የባቡር መስመር ላይ በሐዲዶችና በመጋዘን የተከማቹ ንብረተቶች ላይ ተደጋጋሚ የዘረፍ ሙከራ እየተካሄደበት መሆኑ ተጠቆመ፡፡ ፖሊስ መሠረተ ልማቱንም ሆነ በግንባታ የሚሳተፉ ሠራተኞች ደኅንነት ለማስጠበቅ የተጠናከረ ጥበቃ ማድረጉንና ዘራፊዎችንም ለሕግ ማቅረቡን ገልጿል፡፡

በተለይ በአዳማ ከተማ አካባቢ በመገንባት ላይ ባለው ጣቢያ ተደጋጋሚ ዘረፋ እንደሚፈጽም ተነግሯል፡፡ የጥበቃ ሠራተኞችና ቻይናዊያን ባለሙያዎችም በዘራፊዎች ተኩስ ተከፍቶባቸው እንደነበር ሪፖርተር ሥፍራው ድረስ በመሄድ ማረጋገጡን ዘግቧል።

በግንባታ ላይ የተሰማሩ ሠራተኞች ዘራፊዎች በጦር መሣሪያ ጭምር በሌሊት ካምፑን ሰብረው በመግባት በመጋዘን የሚገኙ ብረታ ብረቶችንና የግንባታ ግብዓቶችን ለመስረቅ ሙከራ እንደሚያደርጉም ጠቁመዋል፡፡

ከአዲስ አበባ-ሜኤሶ ባለው አጠቃላይ መስመር ላይ

አንድ ሻምበል የተጠናከረ ፌዴራል የፖሊስ ኃይል የሚጠበቅ ቢሆንም፣ በአዳማ መጋዘኖች በሚገኙ ቦታዎች ግን ዘራፊዎች ከሠራተኞች ጋር በመመሳጠርም ዘረፋ ለማድረግ መሞከራቸው ተገልጿል፡፡

ግንባታውን እያካሄደ ከሚገኘው የቻይናው ሲአርሲሲ የተገኘ መረጃ፣ ባለፉት ሦስት ዓመታት ከ100 ጊዜ በላይ የዘረፋ ሙከራዎች መፈጸማቸውን ያሳያል፡፡

ሪፖርተር ከፖሊስ መረዳት እንደቻለው፣ ዘራፊዎች በምርመራ ወቅት ሲጠየቁ የዘረፉት ንብረት የአገሪቱ ሳይሆን የቻይና እንደሆነም አድርገው ይቆጥሩታል፡፡

የጥበቃ ሥራውን እያስተባበሩ የሚገኙት ምክትል ኢንስፔክተር እንግዳው ባዬ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በአብዛኛው ሕዝብ ዘንድ የመሠረተ ልማቱን በተመለከተ የተሻለ ግንዛቤ ያለ ቢሆንም፣ በጥቂቶች ዘንድ ያለው ግንዛቤ በተቃራኒው ስለሆነ ሰፊ የግንዛቤ ትምህርት መሰጠት አለበት፡፡

ኩባንያው በበኩሉ በቡድን የተደራጁና የጦር መሣሪያ የታጠቁ ዘራፊዎች በኢትዮጵያውያንና በቻይናውያን ሠራተኞች ላይ በተደጋጋሚ ማስፈራሪያ ሲፈጽሙ፣ በተለያዩ ካምፖች ግንባታ የሚቆምበት ጊዜ እንደነበር ገልጿል፡፡

የአገር አቀፍ የባቡር ትስስር አካል የሆነው የሰበታ-ሚኤሶ የባቡር መስመር ግንባታው በቻይናው ሲአርሲሲ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ 329 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ይኼ ፕሮጀክት በቅርቡ ይጠናቀቃል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ለግንባታው 1.8 ቢሊዮን ዶላር በጀት እንደወጣበት ተዘግቧል።

የሰማያዊ ፓርቲ የምስራቅ ጎጃም ዞን ፀኃፊና በ2007 ዓ.ም ምርጫ የፓርቲው ዕጩ ተወዳዳሪ የነበረው ወጣት ሳሙኤል አወቀ በአሰቃቂ ሁኔታ ተደብድቦ መገደሉ ሲያነጋግር ሰንብቷል፡፡ ወጣት ሳሙኤል አወቀ ሰኔ 8/2007 ዓ.ም ምሽት ላይ ወደ ቤቱ እየገባ በነበረበት ወቅት በሁለት ግለሰቦች ከፍተኛ ድብዳባ ከተፈፀመበት በኋላ ሆስፒታል ውስጥ ነፍሱ አልፋለች፡፡

ወጣት ሳሙኤል ከቀድሞው አንድነት ጀምሮ ሲታገል የቆየ ሲሆን የሰማያዊ ፓርቲ መስራች አባል ነው፡፡ ፓርቲዎ እንደገለጸው በአካባቢው የሚፈፀሙ በደሎችን ለሚዲያ በማጋለጥ ሲያበርክተው ከነበረው ሚና ባሻገር በፓርቲው በነበረው ጠንካራ እንቅስቃሴ ምክንያት በተደጋጋሚ እስርና ድብደባ ተፈፅሞበታል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ በድረ ገጹ ላይ ባወጣው መግለጫ እንደዚህ ብሏል “አንድ ወጣት በተወለደበት ምድር በሕይወት የቆየባቸውን ጊዚያት በስጋት እንዲኖር ከተፈፀመበት ግፍ በተጨማሪ በሕይወት የመኖር መብቱ በአረመኔዎች እጅ ስትነጠቅ የህዝብን ፀጥታና

ደሕንነት እናስከብራለን የሚሉ አካላት በመሃል ከተማ እንኳን ደርሰው ለመታደግ አቅሙም ሆነ ፍላጎቱ አልነበራቸውም. . .

ወጣቱ ሳሙኤል ሰኔ 9 2007 ዓ/ም በምስራቅ ጎጃም ጎንቻ ሲሶእነሴ ወረዳ ሰቀላ ገንቦሬ ቀበሌ አርባይቱ እንስሳ ቤተክርስቲያን ግብዓተ-መሬቱ ተፈፅሟል!

ተገድሏልየሰማያዊው ፓርቲ ዕጩ ሳሙኤል አወቀ

Page 6: Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 … 92.pdf · Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, ... በቀድሞው

ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ Zethiopia Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com 6Yes I want to subscribe Zethiopia Newspaper

Name------------------------------------------------

Address-----------------------------------------------

City................................................................................

State...................Zipcode............................................

Phone,...........................................................................

Email.................................................................................

Starting date...................................................................

For only $40.00

Ze Ethiopia Corp.P.o.box 2049,

Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com

[email protected]

Zethiopia Newspaper

ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ ቤትዎ እንዲላክልዎ ከፈለጉ ከዚህ ቅጽ ጋር የዓመት ደምበኝነት ሞልተው 40 ዶላር ይላኩልን

አሁን ይሄን ደስታ! ሜዳ ውስጥ ወዲያና ወዲህ የሚለው ሰው ሲታይ ደስ ያሰኛል። ሰው የጠማው ወገን የናፈቀው ያገኘውን ሲያገኝ ይፍለቀለቃል። እዚህም እዚያም ይተቃቀፋል። አገር ናሙና ከምትሆንበት ከዚያ ሜዳ የሚገኘውን ደስታ ማንም አይሰጥም። ማንም ደግሞ ሊወስደውም አይቻለውም።

ግን ምነው እንዲህ እንደ ጃን ሜዳው ጥምቀት በዓል መሰባሰባችን ካልቀረ፣ ስንት የላቁ ቁምነገሮቻችንን መተኮስ በቻልንበት ብለን መቆጨታችን አይቀርም። ይሄ ሜዳ ሥርዓት የምንማርበት፣ አገራችንን በቅጡ የምናውቅበት፣ እንዲሁ ሄደ መጣ በላ ጠጣ ተኛ ሳንሆን የላቀ ነገር መስራት የምንችልበት... ቢሆን ማለታችን አይቀርም። አቅም የምናበጅበት ውጤት የምናስመዘግብበት ቢሆን ጥሩ ነበር። ከዚህ አንጻር 32 ዓመት ምን እንደፈየድንበት ራሳችንን የምንጠይቅበት መንገድ ቢኖር ጥሩ በሆነ። ግን ተብሎ ተብሎ ተብሎ ....

እስኪ ይሁን - ይህንንስ ማን አየ! ነጣቂው እየበዛ የሆኑትን ሆኖ ባሉበት መቆየት ራሱ ብርቅ በሆነበት አገር መሰንበት ድል እየሆነልን ባለንበት እየረገጥን ነው ። መሠረታችንን አጽንተን መቆየቱ ግን አጥራችንን ከሚነቅንቁት ያድነናል። ባለቤቱን ካልናቁ አጥሩን አይነቀንቁ የተባለው ተረት ደርሶብን አይተነዋል። ይህ ትምህርት ይሆነን ዘንድ ግን አንዳንድ ነገሮችን መጨዋወት የተገባ ነው።

የአደራ እቃወደ ኳስ ሜዳው የሚሄድ ሰው ሲሄድ ምን እንደሚገጥመው ያውቀዋል። አዲስ ነገር ጠብቆ ሳይሆን አሮጌውን ናፍቆ ነው። እንደ አደራ እቃ ያስቀመጠውን ለማግኘት የመፈለግ ያህል ነው። የሚያውቀውን ሰው ያገኛል። በዚህ ሜዳ ዓይን ተወርውሮ አይስትም። ብዙ የሚያውቃቸው ነገሮች ላይ ያርፋል። የሚያዉቁት ጓደኛ ወዳጅ ዘመድ ይገኛል። በዓይን ብቻ የሚያውቁትም ሰው አለ። ሌላው ቀርቶ በየጊዜው የሚለወጡ ምግብ ቤትን ቬንደሮች ቢኖሩም እንኳ አዲሶቹ ከድሮዎቹ ተለውጠው የሚታዩበት ነገር የለም። ድንኳኖቹ የወንበሮቹ አቀማመጥ አንድ ናቸው። እነዚያው የምናውቃቸው የዛጉ ጠረጴዛዎች የታከታቸው ወንበሮች በህይወት አሉ። የሚገርመው ነገር ፌዴሬሽኑ ከቦታ ቦታ ከስቴት ስቴት ሲሄድ ይዟቸው አይዞርም። ግን ሁሉም ቦታ አንድ ዓይነት ናቸው። በተጠበቀች ወረቅት ወይም በብጣቂ ጨርቅ የማንትስ ምግብ ቤት ተብላ የተጻፈች የንግድ ቤት ምልክት ሁሌም አለች። የሪል ስቴት፣ የቤተክርስቲያናት፣ የኮሙዪኒቲ ማዕከላት፣ የጌጣጌጥ፣ የባህል አልባሳት፣ ሲዲ ዲቪዲ እና ደግሞ ቲሸርት ቲሸርት ቲሸርት..... እና ደግሞ ፍላየር ፍላየር ፍላየር.....

ከዚያ ህጻናትና ታዳጊ ወጣቶቹ የሚያድጉ ቢሆንም ከስር ከስር ደግሞ ሌሎች ይመጣሉ። ግን ሁሉም ይመሳሰላሉ። አለባበሳቸው አካሄዳቸው፣ ነገረ ሥራቸው፣ ያው ከመሆኑ የተነሳ፣ እንዴት ነው እነዚህ ልጆች 32 ዓመት ሙሉ አያድጉም እንዴ አስብሎ ሊያሳስብ ይችላል። ከየትም የሚያንባርቀው ሙዚቃም አዲስ መሆኑ ቢነገርም ያው የሚታወቅ ዜማ ይመስላል። በዚያ ላይ ጩኸቱ ሰዎች ጆሯቸውን እያዋጡ ባይተጋገዙ ኖሮ የአንድ ሰው ጆሮ አይችላቸውም ነበር። ወጣቶቹ ግን ይወዱታል። አንዳንዴም ቆም ብለው ደነስ ደነስ ያደርጉና ደግሞ ሄድ ይላሉ። የትም የሚንከራተተው ዓይናቸው ሜዳ ገብተው እስኪወጡ ምንም ነገር ላይ አያርፍም- ሁሉንም ነገር ለማየት ይሞክራል ሁሉንም ነገር ያጣል...ወይም የሆነ ነገር ይፈልጋል? እነዚህ ልጆች የሚፈልጉትን ነገር ተጨንቆ አውቆ ሊሰጣቸው የሚሞክር ግን ምንም ነገር ያለ አይመስልም።

ሌላው ባንዲራ ነው። ባንዲራ እንኳ ያው ባንዲራ ስለሆነ አዲስ ነገር ሊሆን አይችልም። ዘንድሮ ደግሞ

ፌዴሬሽን እጅግ ትልቅ የሆነ ባንዲራ አሰርቶ ከፊሉን ሜዳ ሞልቶ አንጥፎታል። ቅስትም አሰርቶለታል። በተረፈ ግን ባንዲራችን ከመብዛቱ የተነሳ ወጥና ጥብስ መሆን ነው ያቃታው እንጂ ሁሉ ነገራችን ላይ አለ። ልብሱ ኮፍያው መነጽሩ ሳይቀር አለበት። ሰውነት ላይም ንቅሳት (ታቱ) ሆኗል። እግዜር እየጠበቀን ነው እንጂ ባንዲራን በመውደድና በማክበር መካከል ያለው ልዩነት እስኪገባን ድረስ ያለ ባንዲራ ቀርተን ነበር። ሁሌም ወደ ሜዳ የሚመጣ ሰው ግን ስለባንዲራ ማሰቡ አይቀርም። ነገረ ሁኔታው ሲታሰብ በሆነ ነገር የተቆጨ ትውልድ አንድ ነገር የመግለጽ አመጽ ላይ ያለ ይመስላል!

ከሩቅ የሚታየው የእግር ኳስ ጨዋታ

መቸም ወደ ኳሲቱ የሚሄድ ሰው እጅግም ነው። ቢሆንም አንዳንዴ ማን ከማን እንደሚጫወት መግለጽ ጥሩ ነው። ዓይኑ የትም የትም የሚንከራተት ትውልድ እንደሆነ እንኳን ኳስ አጠገቡ ያለውንም ሰው በቅጡ የሚያይ አይመስልም። መሃል መሃል ላይ ማስተዋወቅ ማሟሟቅ ኳስ ጨዋታ እየተካሄደ መሆኑንም ማስታወስ ይገባል። ለተጫዋቾቹ ሞራልም ቢሆን ይጠቅማል። ሌሎቹንም ያበረታታል። በርግጥ ያንን ሁሉ ሰዓት አቶ ዘውገ ብቻቸውን ጮኸው አይችሉትም- ሌሎች ረዳቶች ያስፈልጓቸዋል። ሲሆን ሲሆንማ አሁን እገሌ ኳስ ይዟል...እሱ ያቀበላትን ኳስ እገሌ በጭንቅላቱ..... የሚለውን በሰማን!

ቅንጅት የሚለው ስም ከቅንጅት ጋር ቀርቶ ይሆን?

በቃ ጥሎብን እንደ ሁሉ ነገራችን እዚህም እዚያም የተቀናጀ ነገር ማየት አልሆነልንም። እዚህም እንዲሁ የሆነ ነገር በቃ ሜዳ ላይ ዝምብሎ መጥቶ የፈሰሰ ይመስላል። በርግጥ እኛን ገርቶ መስመር መስመር ማስያዝ አስቸጋሪ መሆኑ የታወቀ ቢሆንም፣ ፌዴሬሽኑ ግን እንደኛ ህዝብ ሳይሆን ተቋምና ድርጅት ነው። ውስጥ ውስጡን እኛ ሳናውቃቸው የሚያደራጃቸው በርካታ ነገሮች መኖራቸውን ብንገምትም አንዳንዷ ጥቃቅን ነገር ግን ነርቭ ትነካለች። ፌዴሬሽኑ እድሜ ልኩን ከማይሆኑለት ነገሮች አንዱ ቢኖር ለእንግዶች ለንግድ ተሳታፊዎች የይለፍ መታወቂያ (ፓስ) የማዘጋጀቱ ነገር ነው። ቬንደሮች እቃቸውን ተሸክመው በር ላይ ሆነው በሕግ አምላክ በፈጠራችሁ ሲሉ ማስተዋል ከዓመት ዓመት የተለመደ ነው። በተለይም ወዲያና ወዲህ ተሯሩጠው ለሚዘግቡት የሚዲያ ሰዎች ማሰናዳት የሚገባውን ፕሬስ ፓስ አስቀድሞ ማዘጋጀቱ ከ32 ዓመት በኋላም አልተሻሻለም። ዓመት በመጣ ቁጥር፣ “በድምቀት ተከፈተ በድል ተጠናቀቀ” እያልን ልንዘግብ ልናጨበጭብ የምንሄድ ጋዜጠኞችም ብንሆን፣ ማናችሁ ምንድናችሁ? ከማርስና ናችሁ ከጁፒተር? ከሚሉን የፌዴሬሽኑ ኃላፊዎች ጋር ራሳችን ለማስተዋወቅ መጨነቁ ይሰለቸናል። እርግጥ ነው ዘንድሮ ፌስ ቡክ ላይክ ማድረግ የቻለም ሰው ጋዜጠኛ እየሆነ ማስቸገሩ እውነት ነው። ተንጋግተንባቸውም ሊሆን ይችላል። ቢሆንም ቢሆንም ኮሙዪኒቲውን ሊያውቅ የሚገባ ፌዴሬሽን ግን የሚዲያ ሰዎችን ለይቶ ሊያውቅ ይገባል። በተለይ ጋዜጠኞች ፈልገው የማያገኙት የፌዴሬሽኑ የህዝብ ግንኙነት በዚህ ረገድ ቢያስብበት ጥሩ ነው። እንደ ደንቡማ ፕሬስ ኮንፈረንስም ይሰጣል።

በወጪም ቢሆን ፌዴሬሽን በቅንጅት ጉድለት ምን ያህል እየባከነበት እንደሆነ መዘርዘር ይቻላል። ለምሳሌ ስቴዲዮሙን በሚመለከት እንዳለፈው ተመሳሳይ ቦታ የተደረገ ቢሆንም በዚህኛው ዝግጅቱ በከፊል ሳይሆን ሙሉው የስቴዲዮም አካል እንዲከፈት ተደርጓል። በዚህ ወይም በሌላ ምክንያት ባለፈው ጊዜ ለተመሳሳይ ስቴዲዮም ባወጣው ወጪ ላይ ዘንድሮ አንድ መቶ ሺ ዶላር ጣል አድርጎበት ከሆነ ወጪው ከ300ሺ 400ሺ ዶላር ገባ ማለት ነው። ያን ልዩነት ለመመለስ 10 ዶላር የነበረውን የመግቢያ ዋጋ 20 ዶላር አድርጎት ከሆነ እዳውን የሚሸከመው ከፍሎ የሚገባው ሰው ነው ማለት ነው። አንድ ቀን ብቻ ብቅ ለሚል ሰው በርግጥ ገንዘቡ

ምንም ላይሆን ይችላል። የሚመላለሰውስ? የተለያዩ የገቢ ምንጮችን ለማፍራት ዘንድሮ የሙዚቃ ድግሶቹ ላይ እጁን ማስገባቱም እየተሰማ ነው። እጁን ያስግባው በባዶ ሳይሆን ከገንዘብ ጋር ነው። ያተርፈው ይሆን? መጥተው ይጫወታሉ የተባሉ አርቲስቶችም በቪዛ ምክንያት እክል ገጥሟቸው እንደነበር ይታወቃል። የተለያዩ የገቢ ምንጮችን ማቀድ ግዴታው ሊሆን የሚችልበት ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል። እንዲያውም ፌዴሬሽኑ ወደፊት ሊቸገርበት የሚችለው በገንዘብ በኩል ብቻ መሆኑን የሚገምቱ አሉ።

የአስተያየት ቋንጣ!ቆዳው ደንዳና ሆኖ ምንም አስተያየት የማይበግረው ቢኖር ፌደሬሽኑ ነው። ምክንያቱም ብዙ ሰው የማይገባው ፌደሬሽኑ ሥጋ ሳይሆን መንፈስ ነው። መንፈስነቱም በተቋምነት ይገለጻል። መሪዎች ይፈራረቁበታል። ተጫዋቾቹ ይቀያየሩበታል። ቋሚ የሆነ ሰው ባለመኖሩ የሰማው ሲሄድ ያልሰማው ይመጣበታል። ስለዚህ የዛሬ 30 ዓመት የተነገረው አስተያየት አሁን ድረስ ሰሚ ላያገኝ ይችላል። ቢሆንም በፌደሬሽኑ ቦርድና አካባቢው የሚያንዣብቡ የቤት ልጆች ስለሚኖሩ ተስፋ መቁረጥ አያስፈልግም። ቋንጣውንም አስተያየት ቢሆን በየጊዜው እያወጡ መመገብ ያስፈልጋል። በዚያ ላይ ሁሉም በበጎ ፈቃደኝነት (በቮለንቲር) ስለሚሰሩ አይከፈላቸውም። አስተያየት ያለመስማት አንዳንዴም የማበጥ የማንጓጠጥ መንስኤ የሆነውም ይሄ በብላሽ ማገልገል ነው። እንዲያውም አንዳንዶቹ ጊዜያቸውን ገንዘባቸውን ሳይቀር ይሰውበታል። በጎ ፈቃደኝነታቸው የሚያስመሰግናቸው ቢሆንም የለውጥ እንቅፋት ሆኖ መቆየቱም የማይካድ ነው። ፌዴሬሽኑ የአደራ እቃ ሆኖ ባለበት እንዲሄድ ያደረገውም አንዱ መሠረታዊ ችግር ይህ ነው። ሲባል ሲባል ሲባል እንደተኖረው አደረጃጀቱን አስተካክሎ ቋሚ ሠራተኞች ኖረውት የታቀደ ያማረና የሰመረ ሥራ ለመስራት እንዲችል ቢያስብበት ጥሩ ነበር። ሌላው በገንዘብም በምንም ደርጅቶ ሰው ሲያጣ፣ ይኸውኛ ህዝብ እየጎፈረለት ድርጅት የጎደለበት ምክንያቱ ምንድነው?

ሌላው ሲባል የተኖረው ፌዴሬሽኑን ሊያፈርሱ ታጥቀው የተነሱ የተባለው አፋኝ ጨዋታ ነው። እንድ እውነቱ ከሆነ ፌዴሬሽኑን እንዲፈርስ ዛሬ በጸሎት የሚተጉ ወገኖች የሉም ማለት ባይቻልም ፌዴሬሽኑ ሲባል የኖረውን እንዲያስተካክል የጣሩና የተመነጠሩም ብዙ ሰዎች እንዳሉ ይታወቃል። ከዚህም በተለይ

መንገድ ፌዴሬሽኑ ውስጥ ነግሰው ሬዲዮ እየያዙ በየሜዳው ለመንጎራደድ ብቻ ያቺኑ ሥልጣን ፍለጋ ሲሉ የሚያውኩም እንዳሉ አይካድም። ይሄ ሰውየ ካልወረደ ፌዴሬሽኑ ይፈርሳል ይሔ ሰው ካልተመረጠ አለቀለት የሚሉ ዛቻዎችም አልሰሩም። ፌዴሬሽኑ ይሳሳ እንደሁ እንጂ እንደማይፈርስ አሳይቷል። የገባበትን ነፋስ በአግባቡ ማስተንፈስ ካልቻለ ግን መንፈስም ቢሆን መታወኩ አይቀርም።

ከሁሉም በላይ ግን በዚህም ሆነ በዚያ ለለውጥ የሚጓጓ አካል ሊኖር ቢችልም አሸንፎ ወጥቶ አልታየም። መላው የስፖርት ፌዴሬሽን አካል ግን በ32 ዓመቱ የት መድረስ እንደነበረበት ተቆጭቶ ማሰብ ይኖርበታል። ይኼ ይህን አድርገናል ከዚህ ተነስተን እዚህ ደርሰናል እስካሁን በፈተናዎች ውስጥ አልፈን ሳንፈርስ ረጅም ዘመን ቆይተናል ወዘተ ከሚለው የሰነፍ ሰው ጉራ መላቀቅ ይኖርበታል። አንዳንዴ እኮ መድረስ ከሚገባው ደረጃ ሳይደርሱ ረጅም ጊዜ መቆየት ማሳፈሩ እንኳ ቢቀር እጅግም አያኮራም። ሊመሰገኑ ሊበረታቱ ይገባቸዋል የሚባለውን ከንቱ ውዳሴ ብቻ እየጠጡ መኖር ማሰብ ለሚችል ሰው ይደብራል።

በእርግጥ ፌዴሬሽኑ በእድሜ ዘመኑ ብዙ ለውጦችን አፍርቷል። የፌዴሬሽኑ የአንድ ወቅት ዋና ጸሐፊ አቶ ረድኤት ባይለየኝ እንደጻፉት ፌዴሬሽኑ በ1984 ሲጀመር 4 ቡድኖች ቢጀምሩትም ዛሬ 31 ደርሷል። በቅርቡም 32 ይሆናል፤” ይሄ ከተቋቋመበት ዓለማ አንጻር ጥሩ እድገት ነው። ግን እድገት በቁጥር ብቻ አይገለጽም። ያዝ ለቀቅ የሚያደርጋቸው የስፖርት ውድድሮችን ጨምሮ ዝግጅቱን አጓጊና አሳታፊ ሊያደርጉ የሚችሉ የተለያዩ ነገሮችን ማሰብ ይኖርበታል። የፌዴሬሽኑ አባላትም ባኮረፉ ቁርጥ ጥለውት የሚሮጡ ወይም ዳር ሆነው የሚገዘግዙት ሳይሆኑ እዚያው ጸንተው ቤታቸውን ማስተካከልና ድርጅቱን ማነጽ ይኖርባቸዋል።

ፌዴሬሽኑን ለመክፈል የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ ግን በጭራሽ በጭራሽ ባይሞከር ይሻለዋል። ሊቆችን ይዞ ከሚገነጠል ደንቆሮዎቹን ይዞ ቢተርፍልን ይሻላል። እግዜር ጥበቡን የገለጠለን ቀን እናቃናዋለን! የፌዴሬሽኑ መኳኳንቶች ግን ይኽን ዋስትና አድርገው ሳይገበዙ ለለውጥ ቢተጉልን ያለንበትን ዘመንና አገረ አሜሪካን የሚመጥን ድርጅትና ዝግጅት ይኖረናል። እስከዚያው ይኑርልን መልካም በዓል!

32ኛ የኢትዮጵያውያን ስፖርት በዓል በሜሪላንድ በመካሄድ ላይ ይገኛል32ኛው የኢትዮጵያ ስፖርት ፌደሬሽን በሰሜን አሜሪካ ከጁን 28 እስከ ጅላይ 4 2015 በዩኒቨርስቲ ኦፍ ሜሪላንድ በርድ ስቴድየም በመካሄድ ላይ ይገኛል። ካልጋሪና ቶሮንቶ ካናዳን ጨምሮ ከ25 የአሜሪካ ከተሞች ለውድድሩ የመጡ 31 ቡድኖች ተፎካካሪ በሚሆኑበት ከዚህ ውድድር ተጓዳኝ የሚካሄዱ የተለያዩ ክንውኖችን ያካተተው ዝግጅት ባለፈው እሁድ ተከፍቷል። በዓሉን በይፋ የከፈተቱ የፌደሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ተስፋዬ የዘንድሮ በዓል መታሰቢያነት በሊቢያ በግፍ ለወደቁ ወንደሞቻችን መታሰቢያ መሆኑን አስታውቀዋል። እሳቸውንም ተከትለው በፌዴሬሽኑ የተጋበዙ የኃይማኖት አባቶችም በሊቢያና በአገር ጉዳይ ላይ የየእምነታቸውን ቡራኬ ሰጥተዋል። በቅድሚያ “እግዚአብሔር ኢትዮጵያን አይረሳትም” የሚለውን በዝማሬ ጭምር የገለጹት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተከርስቲያን ተወካይ ነበሩ።

የመድኃኔ ዓለም ቤተክርስቲያን ተወካይ ቄስ በሪሁን መኮንን በበኩላቸው ከሊቢያው ሰቆቃ ምን ተምረን በጋር ምን ልንፈጽም እንደሚገባን አጽንዎት ሰጥተው ተናግረዋል። በሰሜን አሜሪካ የሙስሊም ኮሙዩኒቲ ተወካይ ሼክ ሱለይማን ነስረዲን በበኩላቸው እስልምና ወደ አረቡ አገር ከመዛመቱ በፊት መጀመሪያ ወደ ኢትዮጵያ መግባቱን ገልጸው በሊቢያ የተገደሉት ወገኖች የተገደሉት ክርስቲያን በመሆናቸው ሳይሆን ኢትዮጵያዊ በመሆናቸው መሆኑን አበክረው ተናግረዋል። ቀደም ሲል ከተለያዩ ስቴት የመጡት ተጫዋቾች በተየተራ ለህዝቡ ሰላምታ እየሠጡ በሜዳው ያለፉበት ትይንት የቀረበ ሲሆን የተለያዩ ባህላዊ የሙዚቃ ዝግጅቶችም ቀርበዋል። በሚቀጥሉት ተክታታይ ቀናት ህዝቡ ወደ ሜዳው መጉረፍ እንደሚጀምር የሚጠበቅ ሲሆን በተለይ በዓርቡ የኢትዮጵያ ቀን ዝግጅት ላይ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ እንደሚገኝ ይጠበቃል።

በበዓሉ ዝግጅት በተለይም በፌዴሬሽኑ ላይ የተዘጋጀውን አስተያየት ቀጥሎ ያለውን ጽሁፍ ይመልከቱ

እንደው ይኽን ፌደሬሽንአስተያየት

Page 7: Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 … 92.pdf · Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, ... በቀድሞው

ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ Zethiopia Ethiopian American Community News NO.91 June 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia

Send from anywhere you see a Moneygram sign including:

Receive Agents:

Licensed as a Money Transmitter by the Banking Department of the State of New York, licensed by the Georgia Department of Banking and Finance; NMLS #898432; Massachusetts Check Seller License # CS0025, Foreign Transmittal License # FT89432, NMLS # 898432. MoneyGram, the Globe and MoneyGram Bringing You Closer are marks of MoneyGram. All other marks are the property of their respective owners. © 2015 MoneyGram. 0415-81267ZET

800-926-9400 moneygram.com

They gotto enjoy life.

I got to believein endless

love.

It’s amazing how much you receive when you send money.

Job# Client Product File Name Size (W x H) Color Language Artist Start Date Revisions

MG10-2137 Moneygram Ad 0415-81267ZET_Zethiopia_10x21.5.inddLive: 9” x 20.5”

CMYK ENG DA 05/11/15 r01Trim: 10” x 21.5”Bleed: 10.25” x 21.75”

0415-81267ZET_Zethiopia_10x21.5.indd 1 5/11/15 7:29 PM

Page 8: Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 … 92.pdf · Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, ... በቀድሞው

Dial these US numbers from your mobile phone and listen to the

following stations for free!

ከእነዚህ ሬዲዮ ጣቢያዎችየፈለጉትን ደውለው በስልክዎ

መስማት ይችላሉ

Calls only use mobile minutes.

For more information, email: [email protected]

Admas Radio 712.432.8435

AWR Amharic 712.432.9970

BBN Our Voice 857.232.0104

Bereka Broadcasting 712.432.8427

Bilal Communication 712.432.6826

Dallas EthiopianCommunity Radio 712.432.8435

DireTube Radio 716.274.2515

DW Amharic 712.432.2900

ETHIO Diaspora Radio 832.999.5222

Ethiopia Rise and Shine 857.232.0135

ESAT 712.432.7777

Ethiopiawinet 832.225.5387

Fana FM Radio 712.432.9944

FM Addis 97.1

Finote Democracy

231.460.1971

712.832.7010

Helina Radio

Las Vegas 712.432.8498

Hiber Radio

Las

Vegas 712.432.8451

Sheger 102.1 FM 712.432.6885

SBS Amharic 712.432.7701

VOA Afaan Oromo 213.992.4245

VOA Amharic 213.493.0122

VOA Tigrigna 213.493.0272

WENTC 213.992.4363

Zami 90.7 FM 712.832.8090

Connect To Your FavoriteAmharic Programs By Phone

ዋሽንግተን ዲሲ ኮንቬንሽን ሴንተር አጠገብ

ጥሬ ሥጋ - ክትፎ- ጥብስ - የበግ ወጥ

-የጾም በዓይነቱ

ቁርስ ምሳ ራት

ከጧቱ 9 ሰዓት ጀምሮ ክፍት ነው

Page 9: Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 … 92.pdf · Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, ... በቀድሞው

9ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ Zethiopia Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com

32ኛው የሰሜን አሜሪካ ኢትዮጵያውያን ስፖርት በዓል እንግዶችዎን ይዘው ይምጡ

ለጤና የተስማሙ ምግብና መጠጦች!

ከሜትሮ ወጣ እንዳሉ ያገኙናል።

ልዩ ካፌ ሲልቨር ስፕሪንግ

ሜሪላንድ ሲልቨር ስፕሪንግ አራዳው ላይ

Liyu CaféSilver Spring8395 Colesville RD, Suite E Silver Spring, MD 20910

Tel 301 585 1717 or 240 565 8145

ከኢትዮጵያ የመጡ የተለያዩ ቅመማ ቅመሞችና ጥራጥሬዎች

ልዩ ልዩ የእንጀራ ዓይነቶች ከአገር ቤት የመጡ ጭምር

መጠጦች ፣ ምርጥ ሥጋ፣ የፎን ካርዶችካፌ ምግብ ገበያ

ድሮ ሰብዌ የነበረውን አሁን ልዩ ካፌ አድርገነዋል

To go

አንስቶ

ለመሮጥ

መንገድ

ዳር ነው

LENOX ህንጻ ውስጥ እንገኛለን

7835 Eastern Avenue. Suite#207, Silver Spring, MD, 20910

Website: www.sinatravelagency.comEmail: [email protected]

ሲናናTravelናAgencyናየጉዞናናናወኪልሲናና

Your gateway to the World

Writer and broadcaster Lemn Sissay MBE has been elected as the next Chancellor of The University of Manchester.

The 150,000 electorate, comprising University staff, registered alumni and members of the General Assembly chose the award-winning poet from a shortlist of three nominees, which also included Hallé Music Director Sir Mark Elder and former Cabinet minister and Labour peer Lord [Peter] Mandelson.

The election of a new ceremonial figurehead for the University followed the completion of the seven-year tenure of current Chancellor, Tom Bloxham MBE, the founder of Manchester-based property development

company Urban Splash. Lemn will take up his new role on 1 August and an installation ceremony will take place at the University in October.

Lemn is an associate artist at the Southbank Centre, patron of the Letterbox Club and fellow of the Foundling Museum. He is also the author of a series of books of poetry, alongside articles, records, radio documentaries, public art, and plays.

University President and Vice-Chancellor, Professor Dame Nancy Rothwell, said: “The Chancellor of the University, while a ceremonial office, brings with it significant ambassadorial responsibilities in helping to promote the University’s achievements

worldwide, which Tom has done with enthusiasm and dedication throughout his time in office.

“I would like to pay tribute to Tom for his tremendous work over the past seven years and thank all three candidates in the election to be his successor for their interest in the Chancellorship.

“Each one of the nominees had excellent credentials and would have made a fine ambassador for the University.

“My warm and sincere congratulations go to Lemn on his election to be our next Chancellor. I look forward to welcoming him to the University community and working with him to promote

our ambitious plans over the coming years.”

Lemn said: “Reach for the top of the tree and you may get to the first branch but reach for the stars and you’ll get to the top of the tree. My primary aim is to inspire and be inspired.

“I am proud to be Chancellor of this fantastic University and extremely grateful to everyone who voted for me.”

The University also acknowledged the passion and interest shown in the University by both unsuccessful candidates and will be exploring with them other ways in which they may play a constructive role in supporting the University’s agenda going forward.

The Chancellor is the ceremonial head of the University and, as such, acts as a figurehead and an ambassador, working with the President and Vice-Chancellor and other senior officers to promote the University’s achievements, regionally, nationally and internationally.

The Chancellor presides over meetings of the University’s General Assembly and undertakes other ceremonial and representative duties on behalf of the University. The Office is held for a period of seven years and the holder may not be re-elected. (BBC)

Lemn Sissay announced as next University of Manchester Chancellor

Page 10: Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 … 92.pdf · Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, ... በቀድሞው

ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ Zethiopia Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com 10

ኮሙዩኒቲ

Become a driver with Arlington Blue Top Cabs. Easy money and make your own hours.

We provide both rental vehicle and owner operator jobs. We will help you get the licensing done.

Low interest financing on vehicles

Call John at 703 516 7452.

CASH MONEY CASH MONEY- BE YOUR OWN BOSS!!!

በሕክምና ሞያ ለመሰማራት የሚሰጥ ትምህርት

የሞንትጎመሪ ኮሌጅ በሕክምና የሞያ ዘርፍ ከፍተኛ ተፈላጊነት ያላቸው ስራዎችን የሚያስገኙ የአጭር ጊዜ ኮርሶችን በተመጣጣኝ ክፍያ ይሠጣል። እነዚህ የትምህርት ዘርፎችም፦

• ፊዚካል ቴራፒ/

ኦኵፔሽናል ቴራፒ ኤይድ

• ነርስ ሪፍሬሸር

• ሰርቲፋይድ ነርሲንግ አሲስታንት

• የጤና ክፍል አስተባባሪ

• ኢኬጂ (EKG) ቴክኒሻን

• ዲያሊስስ ቴክኒሻን

• ፋርማሲ ቴክኒሻን

• ሰርቲፋይድ ሜዲካል አሲስታንት

• ፕሌቦቶሚ ቴክኒሻን

• እና ሌሎችም

ተጨማሪ መረጃዎችን እና በአማርኛ ቋንቋ እርዳታ ማግኘት ከፈለጉ እባክዎን በኢሜይል አድራሻ [email protected] (ኢሜይል) ወይም በ 240-688-7281 (ስልክ ቁጥር) ሃምራዊት ተስፋን ያነጋግሩ።

የሞንትጎመሪ ኮሌጅ ለሁሉም እኩል ዕድልን የሚሰጥ የትምህርት ተቋም ነው።

ኢሜይል፡ montgomerycollege.edu ስልክ፡ 240-567-5000

በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው ለምትኖሩ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንበሙሉ

በሜሪላንድ ክፍለ ሃገር በሲልቨር እስፕሪንግ ከተማ በ JUNE 20, 2015 ተመርቆ በአልግሎት ላይ የዋለው አዲሱ ቤተ መጽሐፍ የኢትዮጵያ የአማርኛ መጻሕፍት መደርደሪያ ያካተተ መሆኑን ስናበስራችሁ ታላቅ ኩራትና ደስታ ይሰማናል::

በጥቂቶች ይቻላልን ይዘው በተንቀሳቀሱ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ጥረትና ድካም የሜሪላንድ ባለሥልጣናት በዚህ ትልቅና አዲስ በተገነባ የሲልቨር እስፕሪንግ ቤተ መጽሐፍት ለኢትዮጵያውያንን እውቅና በመስጠት በመክፈቻው በዓል መርሐ ግብር ላይ የራሱን መደብ ይዞ እንዲጎበኝ ዕድል በመስጠታቸው በዚህ አጋጣሚ በኢትዮጵያውያን ስም ልናመሰግናቸው እንወዳለን።

ላለፈው አንድ ዓመት በቀድሞው የሲልቨር እስፕሪንግ ቤተ መጻሕፍት በወር አንድ ቀን ከ 3 ዓመት እስከ 7 ዓመት ና ከ 8 ዓመት እሰከ 13 ዓመት የሚገኙትን ኢትዮጵያን አሜሪካን ታዳጊ ወጣቶች በአማርኛና በእንግሊዝኛ ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ፣ ባህልና የመልከዕ ምድር አቀማመጥ የሚገልጹ መጽሐፍትን የማንበብ መርሐ ግብር ያስተዋወቀው የኢትዮጵያ ስነ ጽሑፍና ባህል ማስታወቂያ ማህበር እድገቱን በመቀጠል ዛሬም በአዲሱ የቤተ መጽሕፍት ህንፃ ከላይ የተጠቀሰውን መጽሐፍ የማንበብ መርሐ ግብሩን አጠናክረን እንደምቀጥል ልንገልጽላችሁ እንወዳለን። ይህ ያገኘነው እውቅና እንዲጸና ቤተ መጽሐፍቱ የእኛን የኢትዮጵያውያንን ተሳትፎና ተጠቃሚነትን ማየትና ማረጋገጥ ይፈልጋል።

ስለዚህ ይህንን በጥቂቶች ወገኖቻችን ጥረትና ድካም ያገኘነውን እውቅናና ትልቅ እድል አብቦ ፍሬ እንዲያፈራ ለልጆቻችንም በራሳቸው የመተማመን አቅም የሚያጎለብት የወደፊቱን ብሩህ ተስፋ የሚፈነጥቅ እንዲሆን ዛሬ ከሁላችን ኢትዮጵያውያን የሚጠበቁ ጥቂቶቹንና ቀላሎቹን በመጥቀስ ትብብራችሁን እንጠይቃለን።

1. የቤተ መጻሕፍት መታወቂያ ካርድ በማውጣት መጽሐፍ ተውሳችሁ እንድታነቡ፣

2. በየሁለት ወሩ ቅዳሜ ቀን በሚካሄደው የልጆች የኢትዮጵያ መጽሐፍ ንባብ መርሐ ግብር ላይ ልጆቻችሁን እንድታመጡ፣

3. የኢትዮጵያ መጽሕፍት ያላችሁ ለቤተ መጻሕፍት እንድትለግሱ በዛሬዎቹ ፍሬዎች በነገዎቹ ኢትዮጵያውያን አበቦች ልጆቻችን ስም ትብብራችሁን እንጠይቃለን።

የኢትዮጵያ ስነ ጽሑፍና ባህል ማስታወቂያ ማህበር

Anniversary

ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ

202 518 0245

Page 11: Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 … 92.pdf · Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, ... በቀድሞው

ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ Zethiopia Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com 11Hammond: Andy Tsege detention ‘undermining UK-Ethiopia relations’Ethiopia’s detention of a British man in a secret location for the past year is ‘undermining’ the UK’s ‘much valued’ bilateral relationship with that country, the Foreign Secretary has said.

In a statement released last week, Philip Hammond revealed that he spoke yesterday with the Ethiopian Foreign Minister, Dr Tedros Adhanom

Ghebreyesus, about the fate of Andargachew ‘Andy’ Tsege, a father of three from London who was abducted and forcibly transferred to Ethiopia on 23rd June 2014. Mr Tsege has been held at a secret location ever since, under a sentence of death which was handed down in absentia in 2009 on political charges, related to his involvement with Ethiopia’s opposition movement. He has been denied access to a lawyer, and the British Ambassador has never been allowed to visit him at his place of detention, or been allowed to know where he is held.

Torture is common in Ethiopian prisons, and there are concerns that Mr Tsege is being mistreated. After a recent meeting with him, the Ambassador reported that his mental state appears to have seriously deteriorated.

Following the call, the Foreign Secretary

said he was “deeply concerned that, a year after he was first detained, British national Andargachew Tsege remains in solitary confinement in Ethiopia without a legal process to challenge his detention. I am also concerned for his welfare and disappointed that our repeated requests for regular consular access have not been granted, despite promises made.”

Mr Hammond added that he had told his Ethiopian counterpart that “Ethiopia’s failure to grant our repeated and basic requests is not acceptable. I informed Dr Tedros that the lack of progress risks undermining the UK’s much valued bilateral relationship with Ethiopia.”

Human rights organization Reprieve, which is assisting Mr. Tsege and his family, is asking the UK government to demand his release, in line with international law. However, the Foreign Office has refused to do so, instead focusing – so far unsuccessfully – on

requesting regular consular access to Mr. Tsege, and for ‘due process’ to be followed in his case. The last week statement again stops short of calling for Mr Tsege’s release.

Ethiopia defends detention of opposition Briton, Getachew Reda, an adviser to Ethiopia's prime minister, told Reuters Friday officials had been cooperating with Britain, which was aware of Andargachew's condition.

"The grim stories some are trying to paint are absolutely groundless ... We do not want to let this stand in the way of our relations," Getachew said

"But if the unconditional release of a convicted terrorist is what our British partners ask of us as a condition for maintaining our productive cooperation, it would simply be unfortunate," Getachew added. "It is our belief that they understand this."

“The timing, and the symbolism of Obama’s trip, would “further solidify the image that America stands behind Africa’s autocrats.” Jeffrey Smith of the Robert F. Kennedy Center for

Justice & Human Rights.

Obama is Under fire for visiting Ethiopia

Human rights groups and a leading US newspaper are criticising President Barack Obama’s planned visit this month to Ethiopia.

“It’s almost unfathomable that he would make time for an entrenched human-rights abuser such as Ethiopia while cold-shouldering the nation that just witnessed a historic, peaceful, democratic change of power: Nigeria,” the Washington Post declared in a June 24 editorial.

The Obama administration has previously rebuked Ethiopian authorities for repressive practices. But the US also recently praised Ethiopia for “strengthening its democracy” and has remained silent on the results of elections last month that saw the ruling party, in power for nearly 25 years, capture every seat in the 547-member parliament.

Sarah Margon, Washington director for Human Rights Watch, called that outcome “ridiculous” and likened it to the results of sham elections in the former Soviet bloc.

“We’re disappointed the president is going to Ethiopia,” Ms Margon said in an interview with The East-African. “It’s only going to be seen as, and played by the Ethiopian government as, a reward.”

Human Rights Watch has “no problem” with Mr Obama’s scheduled visit to African Union headquarters in Addis Ababa, Ms Margon added. The US media often portrays Ethiopia as “a success story,” she said, when in fact “it’s a human-rights disaster.”

Some analysts suggest that the US leader’s decision to meet with Ethiopia’s rulers reflects the overriding priority that Washington assigns to counter-terrorism initiatives in East Africa.

Ethiopia contributes nearly 4,500 troops to the 22,000-member African Union force fighting Al Shabaab in Somalia.

The US maintains a base in eastern Ethiopia from which it flies Predator drones over parts of the Horn of Africa. Ethiopia was also reportedly among the sites where the CIA operated secret prisons for interrogating suspected members of Al Qaeda.

Some US businesses are eager to invest in Ethiopia, a country of 94 million people that has recorded significant economic growth in recent years. The Washington-based Corporate Council on Africa is holding its bi-annual US-Africa Business Summit in Addis Ababa in November.

“A decade-long campaign by Ethiopia’s government to silence dissent forcibly has left the country without a viable political

opposition, without independent media, and without public challenges to the ruling party’s ideology,” Freedom House, a New York-based NGO, commented last week.

The organisation noted that of the $400 million in projected US aid to Ethiopia’s “oppressive regime” this year, only $2 million is focused on promoting democracy and human rights.

“Ethiopia is also one of the world’s leading jailers of journalists,” the Washington Post noted in its editorial.

The newspaper argued that Mr Obama’s planned meetings with Ethiopian officials contradicts his declaration of support for African democracies during a visit to Ghana in 2009. “Africa doesn’t need strongmen,” the US president said on that occasion. “It needs strong institutions.”

Mr Obama’s trip to Ethiopia will send “the opposite message, in essence validating Ethiopia’s sham elections and rewarding a regime that has shown no intent to reform,” the Post’s editors wrote.

“Six years after his idealistic speech in Ghana, Mr Obama is sending a message to Africa that democracy isn’t all that important after all.”

(Theeastafrican)

Gedion Zelalem is making the most headlines of his life recently with the entire hubbub about choosing to play for the United States and being included in the U20 side and being the future face of United States football.

The German-born, Maryland-raised Arsenal wunderkind was handed his first start in a US uniform early last month as the US U-20 national team met New Zealand in their second match of the U-20 World Cup, and he did not disappoint.

SB Nation reports that the Berlin-born midfielder looked “calm and confident on the ball with the ability to pick out a precise pass. His lack of physical strength was noticeable at times.”

Zelalem recently said that he believes he is good enough to play for Jurgen Kilnsmann’s senior side and it won’t be long before he gets called up if these skills are anything to go by. The 18-year-old has previously been touted as the ‘next Cesc Fabregas’ and despite making just two senior cameos for the Gunners over the past 18 months

US national team boss Klinsmann echoed Zelalem’s statement in March by saying that the teenager was good enough to walk straight into his squad.

“I think he’s already at a level that he can definitely play on the senior team. He’s a special player.” Jurgen Klinsmann told ESPNFC.

The talented youngster has impressed for the United States during this summer’s U20 World Cup and has been tipped to make a breakthrough into Arsene Wenger’s squad next season.

The 18-year-old, who was born in Germany but plays for the United States, made his first-team debut in January 2014 when he replaced Alex Oxlade-Chamberlain during

Arsenal’s FA Cup fixture against Coventry.

Zelalem, who is contracted with the Gunners until 2017, admits he will opt for a loan move this summer if he can’t make a breakthroug

Although he has the potential to someday play for Germany’s elite national team, Zelalem’s heart is more American than German. He has not lived in Germany since 2006. He speaks English without a German accent. He grew up in an American suburb, attended American public schools and played club soccer in Maryland before relocating to London two years ago to be closer to the Arsenal set-up. Choosing United States the Turning Point in Gedion Zelalem's Arsenal Careerwhen the ball is on this kid’s feet, the

US always look a threat to score.

U-20 World Cup star Gedion Zelalem

Choosing United States the Turning Point in Gedion Zelalem's Arsenal Career

Ethiopia is building the continent’s biggest wind farms by taking advantage of the strong winds blowing over Adama rocky hills in the country’s highlands.

According to a new report by AFP, the government of Ethiopia sees Adama region as a perfect location for the construction of three wind farms, the first of which has been already made operational.

Solomon Yismaw, the engineer, who is in charge of 102 Chinese-built turbines, each 70-meter high, which are used in the project, said “In February, during the dry season, it is even difficult to stand here.”

The first Adama wind farm was inaugurated almost a month ago with the capacity to produce 153 megawatt (MW) of electricity, which makes it the largest wind farm in sub-Saharan Africa.

According to local officials, the hills in Adama region, which is located 100 kilometer southeast of the capital, Addis Ababa, stand 2,000 meters above the sea level.

Ethiopia building largest wind farms in Africa

Page 12: Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 … 92.pdf · Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, ... በቀድሞው

ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ Zethiopia Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com 12

ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com

ታሪክና ሥነፅሁፍዓለማየሁ ገ/ሕይወት

ዶ/ር ፍጹም አቻምለህ ዓለሙ ከሃገንጋሪ ቡዳፔስት በህግ የመጀመሪያ ዲግሪውን ያገኘው እ.ኤ.አ. በ1988 ነበር። ከኢትዮጵያ ለትምህርት ከሄደበት ሃንጋሪ ትምህርቱን እንደደረስ ለተደማሪ ትምህርት በቡዳፔስት ከሚሰራበት የሰብዓዊ መብት ድርጅት ስኮላርሺፕ አግኝቶ ወደ አሜሪካ መጥቷል። እንደገና ወደ አውሮፓ ቡዳፔስት በመመለስ በሃንጋሪ ታዋቂ ለሆነ አንድ ሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ጠበቃና የፕሮጀክት ማኔጀር ሆኖ ሠርቷል። ከ1996 ጀምሮ ወደ አሜሪካ በምመጣት በተለያዩ ቦታዎች ሲሠራ ከቆየ በኋላ ከዲሴምበር 2003 ጀምሮ የራሱን የፍጹም አቻምየለህ የጥብቅና ድርጅት አቋቁሞ እየሠራ ነው።

ዶ/ር ፍፁም አቻምየለህ

አንዳንድ ነገሮች ስለሕግ

ውድ ወንድሜ ሆይ፣ ከረዥም ዓመታት በኋላ መልእክትህ ሲደርሰኝ በጣሙን ነው ደስ ያለኝ። በእንዲህ ያለ ስሜትን በሚነካ አሳዛኝ ሁኔታ ውስጥ ሆነን መገናኘታችን በእርግጥ ያሳዝናል።

በሃገራችሁ በነበርንበት ጊዜ ለሞዛምቢክ የዜና አገልግሎት ስትሠራና ፊት የቴምፖ ኋላ ላይ ደግሞ የኖቲሲያስ መፅሄቶች አዘጋጅ ሆነህ አውቅሃለሁ። ሞዛምቢክ ለጓዶቼና ለእኔ ለራሴ ያደረገችልንን የወዳጅነት ድጋፍ ከቶም ልረሳው አልችልም። እንደውም ሞዛምቢክ ሁለተኛ ሃገሬ ሆናለች። አሁንም ወደፊትም ናት።

በሞዛምቢካውያን ሞትና በአጠቃላይም ሃገራችን ውስጥ በውጪ ሃገር ተወላጆች ላይ በደረሰው ጥቃት ልብህ እንደተነካ ደብዳቤህ ያመለክታል።

ባለፉት ሳምንታት በተከሰተው በዚህ አሳዛኝና ትርጉም የለሽ ግድያ የሰባት ሰዎች ህይወት በማለፉ ደቡብ አፍሪካውያንም ልባቸው ተሰብሯል። ከነዚህ ውስጥ ሶስቱ ደቡብ አፍሪካውያን ሲሆኑ አራቱ የውጭ ዜጎች ናቸው። እግዚአብሔር ነፍሳቸውን በገነት ያሳርፋት። የነሱ አሳዛኝ ሞትም ሰላምን በማስፈንና የአመፅን መንገድ በመዝጋት ጥረታችን አንድ ያድርገን:: ባለፈው ሳምንት በደርባን የታየውን ጥቃት የቀሰቀሰው የሥራ ማቆም አድማ የመቱ ደቡብ አፍሪካውያንን አባሮ የውጭ አገር ዜጎችን በቀጠረ አንድ አሰሪ ጥፋት እንደሆነ የደረሰን መረጃ ያመለክታል:: ደቡብ አፍሪካ ውስጥ የሥራ ማቆም አድማ በመቱ ሠራተኞች ምትክ የሚደረግ ቅጥር ብዙውን ጊዜ ቁጣ ይቀሰቅሳል:: እንዲህ አይነቶቹ በሠራተኞች መካከል ግጭት የሚያስከትሉ ሁኔታዎች እንዲታረሙ ከሃገሪቱ የሠራተኛ ማህበራት ጋር እየሠራን ነው:: በጥር ወር በሶዌቶ የተፈጠረውን የአመፅ ተግባር ያነሳሳው ደግሞ አንድ ወጣት ደቡብ አፍሪካዊ ባልሆነ የሱቅ ሠራተኛ በጥይት ተመቶ ክፉኛ በመቁሰሉ ነው::

ይህ ወቅት ለሃገራችንም ሆነ ለህዝቧ እጅግ አስቸጋሪ ወቅት ነው:: በሚሊዮን የሚቆጠሩት ሰላም ወዳድ ደቡብ አፍሪካውያን የውጭ ዜጎችን እንደሚጠሉ ተደርገው በሃሰት በመወንጀላቸው በጣም አዝነዋል:: ደቡብ አፍሪካውያን የውጭ ሃገር ተወላጆችን ፈፅሞ አይጠሉም:: ጥቂት ወገኖች በፈፀሙት የጥፋት ተግባር ሃምሳ ሚሊዮን ያህልን ህዝብ በጅምላ መወንጀል አግባብ አይደለም::

ከ1986 ዓ.ም. ጀምሮ ሃገራችንን ለመገንባትና የዘር መድሎውን ሥርዓት አስከፊ ገፅታ ለመለወጥ ተግተን ሠርተናል:: የማንኛውም ዜጋ የኑሮ ዋስትና፣ ሰብዓዊ መብት፣ እኩልነትና ክብር የተረጋገጠበት ማህበረሰብ ለመፍጠር ያደረግነው ጥረት ፍሬ አሳይቷል:: አሁንም ቢሆን ከማናቸውም አይነት መድሎ ነፃ የሆነ ማህበረሰብ የመገንባቱን ጥረት እንቀጥልበታለን:: ይህንንም የምናደርገው በቆዳህ ቀለም፣ በቋንቋህ፣ ወይንም በጎሳ ማንነትህ ምክንያት የሚፈፀም አድሎ ምን ያህል እንደሚያቆስል ስለምናውቀው ነው::

በውቢቷ ሃገራችሁ በስደት ላይ በነበርኩበት ወቅት ሞዛምቢካውያን ያደረጉልኝን መስተንግዶና እንክብካቤ አስታውሰኸኛል:: ዓለማቀፋዊ የትግል አንድነትና ወዳጅነትን መሥርተን የዘር መድሎውን ሥርዓት ለመጣል ባደረግነው ትግል ተጠቃሚ መሆናችን እውነት ነው:: አፍሪካውያን ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በተለይ ካለቻችው ውስን ሃብት አካፍለውናል:: በርካቶች ለነፃነት የምናደርገውን ትግል ደግፈው ህይወታቸውን አጥተዋል:: የማቶላው አደጋ ለዚህ ቅርብ ምሳሌ ነው:: ለዚህም ነው ወድ ሃገራችን በህጋዊ መንገድ የሚመጡ አፍሪካውያን ወንድሞቻችንና እህቶቻችንን በደስታ የምንቀበለው:: ስደተኞችን የምናስተናግድበት ፖሊሲያችንም በጣም ዘመናዊ በመሆኑ ስደተኞችም ሆኑ የደህንነት ስጋት ያለባቸው ስዎች ወደ ሃገራችን ሲመጡ ከህብረተሰቡ ጋር እንዲቀላቀሉ ነው የምናደርጋቸው:: ከዜጎቻችን ጋር አብረው ይኖራሉ:: የማህበረሰባችን አካል ይሆናሉ::

በርካታ ሞዛምቢካውያን ከሞቱበትና የዘር መድሎው ሥርዓት ወታደሮች ካደረሱት አሳዛኝ የማቶላ ጥቃት በኋላ ፕሬዚደንት ሳሞራ ማሼል እንዳሉት አንድ ህዝብ ነን:: ሞዛምቢካውያንና ደቡብ አፍሪካውያን እንዲሁም የሞዛምቢክ ነፃነት ግንባር (Frelimo) እና የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ (ANC) ታሪክ የማይሽረው ፅኑ የሆነ ወዳጅነት አላቸው:: ይህም ወዳጅነት አብረን በመኖራችን፣ አብረን በመሥራታችን፣ አስከፊውን የዘር መድሎ ሥርዓትም አብረን በመታገላችን የተፈጠረ ነው::

ከዘር መድሎው ሥርዓት ሊሰነዘርባት የሚችል ጥቃት ቢኖርም የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ ታጋዮችና ተዋጊዎች ድንበር አቋርጠው በምስጢር ወደ ደቡብ አፍሪካ እንዲገቡና እንዲታገሉ ሞዛምቢክ ያደረገችውን ያላሰለሰ ጥረት በሚገባ ገልፀኸዋል:: በመጀመሪያዎቹ የፀረ ቅኝ

ስደት፣ የጠቢብና ፖለቲከኛ ጭውውትበአፕሪል 2015 መጨረሻ ገደማ (እንዳለንበት ሃገር የዘመን አቆጣጠር) የዚህ ፅሁፍ አቅራቢ በሥራ አጋጣሚ ሞዛምቢክ ውስጥ ተገኝቶ ነበር። በወቅቱ በደቡብ አፍሪካ በሚኖሩ የውጭ ተወላጆች ላይ ተከታታይ ጥቃቶች ከመፈፀማቸው ጋር ተያይዞ ጉዳዩ የብዙዎች መነጋገሪያ ሆኖ ነበር። ከዚህም በላይ የብዙዎችን ቀልብ የሳበው ሞዛምቢካዊው ደራሲ ሚያ ኩቶ ለደቡብ አፍሪካው ፕሬዚደንት ለያዕቆብ ዙማ የፃፈላቸው ግልፅ ደብዳቤና ከፕሬዚደንቱ የተላከለት መልስ ነበር። ደብዳቤዎቻቸው ‘Daily Maverick’ በተሰኘው ዕለታዊ የድረ ገፅ ጋዜጣ ላይ ወጥተዋል። ሁለቱ ሰዎች የቀደመ ትውውቃቸውንና ደቡብ አፍሪካ የገጠማትን ፈተናና መፍትሄውን አስመልክቶ ያደረጉትን የሃሳብ ልውውጥ እንደሚከተለው በአማርኛ ቋንቋ ተርጉመነዋል።

ይድረስ ለውድ ፕሬዚደንት ዙማ፣

ውድ ፕሬዚደንት፣ ዛሬ ደቡብ አ ፍሪካ ውስጥ በውጭ ሃገር ተወላጆች ላይ የሚፈፀመው ኋላ ቀር የሆነ ጥቃት

በ”ሌሎች ዜጎች” ላይ ብቻ የተሰነዘረ አይደለም። በደቡብ አፍሪካ በራሷም ላይ የተቃጣ በትር ነው። ደቡብ

አፍሪካውያን “ቀስተ ደመናዊ ሃገር” ብለው ከአንድ ዓሠርት ዓመት በፊት በኩራት ይጠሯት በነበረችው ሃገር ላይ የተሰነዘረ ጥቃትም ነው። የተወሰኑ ደቡብ

አፍሪካውያን የእናት ሃገራቸውን ስም እየበከሉት ነው።

በ1980ዎቹ ገደማ ሞዛምቢክ ውስጥ የፖለቲካ ጥገኛ ሆነው በማፑቶ አካባቢ ሲንቀሳቀሱ እናስታውስዎታለን። አልፎ አልፎም በጁልዬስ ኔሬሬ ጎዳና እየተገናኘን እንደመልካም ጎረቤታሞች የእግዜሩን ሰላምታ እንለዋወጥ ነበር። አንዳንዴም በዘር መድሎ ላይ የተመሠረተው የአፓርታይድ ሥርዓት እንደሚያሳድድዎ ስለማውቅ በምን አይነት ስጋት ውስጥ ይኖሩ ይሆን እያልኩ አስብም ነበር። በርስዎም ላይ ሆነ በትግሉ ውስጥ በሚሳተፉት ጓዶችዎ ላይ የሚሸረበውን ሴራ እያሰቡ እንቅልፍ የሚያጡባቸውን ሌሊቶችም አስብ ነበር። ያም ሆኖ አንድ ቀን እንኳ በጠባቂ ታጅበው ሲሄዱ ያየሁበትን ጊዜ አላስታውስም። እንደ እውነቱ ከሆነ ጠባቂዎቻችሁ እኛ ሞዛምቢካውያኑ ነበርን ማለት ይቻላል። ለዓመታት ከጥገኝነት ያለፈ እንክብካቤ አድርገንላችኋል። ቤት ሰጠናችሁ። የኛ ደህንነት ለአደጋ አጋልጠን የእናንተን ደህንነት አረጋገጥንላችሁ። ይኼንን ደግነት መቼም ሊረሱት አይችሉም። እኛ አልረሳነውም።

ለደቡብ አፍሪካ የነፃነት ትግል ላደረግነው ድጋፍ ምናልባትም ከሌሎች ጎረቤት ሃገሮች በበለጠ ሞዛምቢክ ዋጋ ከፍላበታለች። ደካማው ኢኮኖሚያችን ጭራሽ ደቀቀ። ድንበራችን ተደፈረ፣ በቦንብም ተደበደበ። ሞዛምቢካውያንም ከድንበራቸው ባሻገር በኩል ያሉ ወንድሞቻቸውን ለመከላከል ሲሉ መስዋዕትነትን ከፈሉ። ለእኛ ውድ ፕሬዚደንት ድንበር አልነበረም። ዜግነትም አልወሰነንም። ሁላችንም አንድ ዓላማ ይዘን የታገልን ወንድማማቾች ነን። የዘር መድሎው ሥርዓት ሲወድቅም ከድንበር ወዲህም ሆነ ማዶ ደስታችን እኩል ነበር።

ሞዛምቢካውያን ስደተኞች፣ የማዕድን ቁፋሮ ሠራተኞችና አርሶ አደሮች በጎረቤት ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ከባርነት ባልተናነሰ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ለዘመናት ሲሠሩ ኖረዋል። እነዚሁ ሠራተኞች ለደቡብ አፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት አስተዋፅኦ ያደረጉ ናቸው። ዛሬ ጥቃት የሚደርስባቸው የነዚሁ ሠራተኞች አስተዋፅኦ የሌለበት አንዳችም ሃብት በሃገርዎት ውስጥ የለም።

በነዚህ ሁሉ ምክንያቶች የተነሳም ዛሬ በሃገርዎ ውስጥ እየተካሄደ ያለውን ነገር መገመትም ሆነ ማሰብ ይከብዳል። የዘር መድሎው ሥርዓት ነፍጠኞች የነፃነት ታጋዮችን በሃገር ውስጥም ሆነ በውጭ ባሳደዱበት የጭካኔ መንገድ ሞዛምቢካውያን በደቡብ አፍሪካ ጎዳናዎች ይሳደዳሉ ብሎ ማሰብ ይከብዳል። ዛሬ በኛ ላይ የደረሰው ጭንቀትና መከራ ያኔ እርስዎ ላይ ይደርስ ከነበረው ፈተና የከፋ ነው። የእርስዎ የግፍ ሰለባነት ላመኑበት ታላቅ ዓላማ ሲሉ ወደውና ፈቅደው የገቡበት ነው። ዛሬ በሃገርዎ ግፍና መከራ የሚፈፀምባቸው እነዚያ ምስኪኖች ግን ጥፋታቸው የሌላ ሃገር ዜጎች ሆነው መገኘታቸው ብቻ ነው። ወንጀላቸው ሞዛምቢካዊ መሆናቸው ብቻ ነው። የተላለፉት በደላቸው ደቡብ አፍሪካዊ አለመሆናቸው ብቻ ነው።

እርግጥ ነው አንዳንድ እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው። በቂ ሆነው ግን አልተገኙም። በዚያ ላይ ከመሸ የተጀመሩ ናቸው። የደቡብ አፍሪካ መሪዎች የመሰላቸውን መናገር ይችላሉ። ሳናውቀው ድንገት የሆነ ነው ሊሉ ግን አይችሉም። ታሪክ ራሱን እንዲደግም እድል ተሰጥቶታል። ጥላቻን የሚያስፋፉ ድምጾች አየሩን ሞልተውት ነበር።

ለዚህም ነው በሞዛምቢካውያን ወገኖቻችን ስም ይህን እንደሰደድ እሳት ሊስፋፋና መላ አህጉሯን ሊያዳርስ የሚችል፣ የበቀልን ስሜት ከደቡብ አፍሪካ ድንበር ባሻገር እየፈጠረ ያለ ሁኔታ በአስቸኳይ አንዲያስቆሙ የምንማፀንዎ። ሁኔታው የፀጥታ ሃይሎችን ከማሰማራት ጀምሮ ጠንካራ፣ አፋጣኝና ሁለንተናዊ የሆነ እርምጃ መውሰድን ይጠይቃል። ዋናዋ የጥቃቱ ሰለባ ደቡብ አፍሪካ ራሷ ናትና።

ክቡር ፕሬዚደንት፣ ይህን መሰሉ ወንጀል በፀጥታ ሃይሎች እርምጃ በቁጥጥር ሥር ሊውል እንደሚችል ከእኛ በተሻለ እርስዎ ያውቃሉ። የወቅቱ ሁኔታ ግን ተመሳሳይ ችግሮች ዳግም እንዳይፈጠሩ ለመከላከል የሚያስችል እርምጃ መውሰድን ይጠይቃል። እንዲህ አይነት የወንጀል ተግባራት መቼውንም ቢሆን መደገም የለባቸውምና!

ለዚህ ደግሞ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሄ ሊያመጡ የሚችሉ እርምጃዎችን መውሰድ ያስፈልጋል። ያለፈውን ስህተት ለማረም የሚያስችሉ ህዝባዊ የመማማሪያ መድረኮችን በአስቸኳይ መፍጠር ይገባል። በህዝቦቻችን መካከል የአንድነትና የወንድማማችነትን ስሜት መፍጠርና በጋራ የተወጣነው የትናንቱ የተጋድሎ ታሪካችን ትዝታው እንዳይጠፋ ማድረግ ይቻላል።

እንደ ከያኒያን፣ እንደባህልና የማህበራዊ እሴቶች ባለቤቶች፣ ከደቡብ አፍሪካ ጠቢባን ጋር በአንድነት ቆመን ይህንን ፊታችን የተጋረጠ ፈተና ለመቋቋም ዝግጁ ነን። እምነታችን እምነታቸው ከሆነው አያሌ የደቡብ አፍሪካ ማህበረሰብ አባላትም ጋር አብረን ለመሥራት እንፈልጋለን። ይህንን አሳዛኝና አሳፋሪ ሁኔታ ወደላቀና የህዝቦቻችንና የሃገሮቻችንን ክብር ወደሚያሳይ ተግባር ልንለውጠው እንችላለን። እንደ ከያኒያንና ደራሲያን ከመልክዓ ምድራዊ ግንኙነት ሳይሆን ከወል ማንነታችንና ከተጋራነው ታሪካችን የሚፈልቅ ፅኑ የጉርብትና መንፈስ እንዲበለፅግ ተግተን ለመሥራት ያለንን ቁርጠኝነት ለመግለፅ እንወዳለን።

ሚያ ኩቶ - አፕሪል 17/ 2015

ግልፅ ደብዳቤ ለሞዛምቢካዊው ደራሲና ባለቅኔ ሚያ ኩቶ

ወደ ገጽ 14

ጉዲፈቻ (Adoption) ማለት በጎልማሳና በህጻን ልጅ መካከል የሚደረግ፣ የወላጅ-ልጅ ዝምድናን የሚመሰርት ሕጋዊ ግንኙነት ነው።

አሜሪካዊ ዜጋ፣ ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ ያለው፣ ጥገኝነት የተሰጠው፣ ወይንም የጥገኝነት ማመልከቻው በሂደት ላይ ያለ ሰው ከ16 ዓመት በታች የሆነን ልጅ በጉዲፈቻ መቀበል ይችላል። ያንን ህጻን ከጉዲፈቻ ተቀባዩ ወላጅ ጋር የሥጋ ዝምድና (ወንድም፣ እህት፣ የእህት፣ወንድም ልጅ፣ የአጎት የአክስት ልጅ ወዘተ) ቢኖረውም ባይኖረውም በጉዲፈቻ መቀበል ይችላል።

በኢምግሬሽን ህግ መሰረት ጉዲፈቻ ተቀባይነት የሚኖረው ሕጻኑ በሚኖርበት አካባቢ ያለ አጥቢያ ፍርድ ቤት (ኢትዮጵያ ከሆነ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት) ለጉዲፈቻ የገባውን ማመልከቻ ህጻኑ 16 ዓመቱ ከመሙላቱ በፊት ካፀደቀው ነው። ህጻኑ ከ16 ዓመት በላይ ከሆነ ግን ጉዲፈቻው ምንም ዓይነት የኢምግሬሽን ጥቅም አያመጣም።

በተለምዶ እቤት ውስጥ ከህጻንነት ጀምሮ ያሳደጉትን ልጅ ለማስመጣት ማመልከቻ ቢያስገቡ፤ ወይም ደግሞ ከቀበሌም ሆነ ከገበሬ ማህበር ወይም ከወረዳ ጽ/ቤት አስፈርመው ደብዳቤ ቢያስመጡ በኢምግሬሽን በኩል ተቀባይነት አይኖረውም። በሕግ ተቀባይነት ያለው ከላይ የተጠቀሰው ዓይነት የፍ/ቤት ውሳኔ ብቻ ነው። እርስዎ እዚህ ሆነው፣ ሌላ አገር የሚኖረውን ህጻንን በውክልና ጉዲፈቻ ሊቀበሉት ይችላሉ። ህጻኑ አሜሪካን አገር ካለ ግን በአካባቢው ያለው የወረዳ የቤተሰብ ፍ/ቤት(Juvenile and Domestic Relation or Family Court) የጉዲፈቻ ማመልከቻውን ሊሰማዎና ሊያጸድቅልዎ ይችላል።

ውሳኔውን በ እጅዎ ከገባ በኋላ፣ የራስዎ የኢምግሬሽን ሁኔታ፣ ወይም ዜጋም ከሆኑ ህጻኑን ወደ አሜሪካን አገር ለማስመጣት፣ማመልከቻ ማስገባ ይችላሉ። ዜጋ ከሆኑ የዘመድ ማስመጫ ፎርም፣ (I130) ከተሰጠዎና ሁለት ዓመት ካልሞላዎት፣ የጥገኛ ዘመድ ማስመጫ ፎርም (I-730) ፣ ዜጋ ከሆኑና በጉዲፈቻ የተቀበሉት ልጅ ወላጅ አልባ ከሆነ፣ (I 600) ማመልከቻ ሊያስገቡለት ይችላሉ።

ጉዲፈቻ የተቀበሉት ልጅ በምን ያህል ጊዜ ወደ አሜሪካ ይመጣል የሚለው ጥያቄ የሚወሰነው ግን እርስዎ ጉዲፈቻውን ሲቀበሉ፣ የሕጻኑ ወላጆች በሕይወት የመኖር አለመኖራቸው ሁኔታ ነው። ሕጻኑ ወላጅ አልባ (Orphan) ከሆነ ማለት ወይም ሁለቱ ወላጆች በህይወት ከሌሉ፣ ወይም አንዱ ወላጅ በሕይወት ከሌለና፣ ሌላኛው ደግሞ ልጅ ማሳደግ የማይችል ከሆነ ወይም ትቶት ከጠፋ (Abandoned) ሕጻኑ ብዙም ወረፋ ሳይጠብቅ ወደ አሜሪካ ሊመጣ ይችላል። ነገር ግን ሁለቱ ወላጆች በሕይወት ካሉ፣ አንደኛው በሕይወት ካለና በሱ ይሁንታ ከሆነ ልጁን በጉዲፈቻ የተቀበሉት፣ የኢምግሬሽን ማመልከቻውን ከማስገባትዎ በፊት ሕጻኑ ከርስዎ ጋር ወይም በርስዎ ቁጥጥር ሥር ለሁለት ዓመት መኖር አለበት። በእርግጥ ይህ ለብዙ ሰዎች ችግር እየፈጠረ ነው። እንደኔ አስተያየት መታወቅ ያለበት፣ የጉዲፈቻ ሕጉ ሲወጣ፣ ታሳቢ ያደረገው ነገር፣ ለጊዚያዊ ሥራ አገልግሎት፣ ውጭ አገር የሚኖሩና ሥራቸውን ጨርሰው የሚመለሱ አሜሪካውያን ቤተሰብ የሌላቸውን፣ ወይንም ያስጠጓቸውን የድሃ ልጆች፣ እንዲያመጡ ነው እንጂ በኛ ሁኔታ ላሉ ሰዎች አይደለም። ይሁን እንጂ ጉዲፈቻው በፍርድ ቤት ከተወሰነ በፊትም ሆነ በኋላ፣ እርስዎ እየተመላለሱ ወይም እዚያው ተቀምጠው ሕጻኑ ከርስዎ ጋር ሁለት ዓመት መኖሩን በበቂ ማስረጃ የሚያሳዩ ከሆነ፣ ሊያመጡት ወይም ሊያመጧት ይችላሉ። የኢምግሬሽን ማመልከቻውን ካስገቡ በኋላ፣ የኢምግሬሽን ቢሮ የጉዲፈቻ ተቀባይ ወላጅ ብቁነትን የሚያሳይ የኑሮ ሁኔት ጥናት(Home Study )ፈቃድ ባለው ድርጅት ወይም ግለሰብ ማስጠናት ይኖርብዎታል። ያ ድርጅት ወይም ግለሰብ እርስዎን ብቁ ነዎት ካልዎት ብሎም ሌሎች መረጃዎችን በበቂ ሁኔታ ካስገቡ ማመልከቻው ተቀባይነት ሊኖረው ይችላል።

ሌላ መታወቅ ያለበት ነገር፣ ከመስከረም 2013 በፊት የኢትዮጵያ መንግሥትና ፍ/ቤቶች ይህን የኑሮ ሁኔታ ጥናት (Home Study )ከፍርድ ቤት ውሳኔ በፊት መጠናቀቅ አለበት ብለው ስላዘዙ፣ ሕጻኑን ከኢትዮጵያ የሚያመጡ ከሆነ ጥናቱን አስቀድመው ማስደረግ ይኖርብዎታል። ከላይ እንደተጠቀሰው ይህ ጥናት የሚካሄደው በኢምግሬሽን ፈቃድ በተሰጣቸው ሰዎች ወይም ድርጅቶች ነው። አጥኚዎች የተቀባዩን የጠቅላላ የኑሮ ሁኔታ ማለት ደመወዝ፣ ሀብት፣ የቤት አያያዝ፣ የጋብቻ ሁኔታ፣ ሌሎች ልጆች መኖራቸውና አለመኖራቸውን፣ ተቀባዩ ከወንጀል ነጻ መሆኑን ወዘተ መርምረው ብቁነቱን ወይም ብቁ አለመሆኑን በጽሁፍ የሚሰጡ ናቸው።

ማመልከቻው በኢምግሬሽን ከተፈቀደ ሕጻኑ የጉዲፈቻ ወላጁን ዓይነት ፈቃድ ያገኛል። - ዜጋ ከሆነ ዜጋ ይሆናል። ቋሚ መኖሪያ ፈቃድ ካለው ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ ያገኛል- ጥገኝነት ካለ ጥገኝነት ያገኛል።

በጉዲፈቻ የሚቀበሉትን ልጅ እንደወለዷቸው ልጆች የመንከባከብ፣ የማሳደግና የሚያስፈለገውን ሁሉ የማድረግ ግዴታ አለብዎ፣ ሕጻኑም ልክ እንደወለዷቸው ልጆች በርስዎ ስም ይጠራል ከልጆችዎ እኩል ሁሉን ነገር ያገኛል፣ ንብረትም ይካፈላል። ጋብቻውን እንኳ ቢፈርስ በሕጻኑ ተቋራጭ (Child Support) መክፈል ይገባዎታል።

ጉዲፈቻ (Adoption)

ኢት. አየር መንገድ ወደ ሎስ አንጀለስ የቀጥታ በረራ ጀመረየኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሎስ አንጀለስ የቀጥታ በረራ ጀመሯል።

አየር መንገዱ ባለፈው ወር መጨረሻ 197 መንገደኞችን በመያዝ ወደ ሎስ አንጀለስ የጀመረው የቀጥታ በረራ ከአፍሪካ የመጀመሪያው አየር መንገድ ያደርገዋል።

ሎስ አንጀለስ በአሜሪካ አህጉር የአየር መንገዱ አራተኛ መዳረሻ ነው። አየር መንገዱ ወደ ሎስ አንጀለስ ሲያቀና በአየርላንድ ደብሊን ከተማ አድርጎ በመሆኑ ይህም የአውሮፓ መዳረሻዎቹን ቁጥር 11 ያደርሰዋል። ገና በመጀመሪያው በረራም በአየርላንድ 7 መንገደኞች ጥገኝነት መጠየቃቸው ይታወሳል።

ዳኛዋን የዘረፈቸው ምስኪኗ የቤት ሠራተኛሬዲዮ ፋና እንደዘገበው የ16 አመቷ ወጣት ከደቡብ ክልል ጋሞ ጎፋ ዞን ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በቤት ሰራተኝነት በልደታ ፍርድ ቤት በሚሰሩት ዳኛ ከተቀጠረች ገና ከሶስት ሳምንቷ ነው። የአዲስ አበባ ኑሮ ሳይመራት አልቀረም። ታዲያ አንድቀን አጋጣሚ ሆኖ እጇ የገባን ቁልፍ ተጠቅማ የዳኛዋን ቁምሳጥን መከፍት በመቻልዋ መበርበር ትጀምራለች።

ያገኘችውን 800 ብር ከሞባይል ስልክ ጋር ሰርቃ ወደ አገሯ ወደጋሞጎፋ ለመመለስ አውቶብስ ላይ ትሳፈራለች።

ታዲያ በመካከሉ መንገድ ላይ የሰረቅችው ሞባይል ስልክ ይጮኽ ጀመረ። ምኑን ከምን አድርጋ እንደምታነሳው ወይም እንደምታጠፋው ግራ ገብቷት ተደነባበረች። መቸም እግዜር ትንሺቱን ሌባ አይወድምና ከጎኗ ያለው ሰው ጠርጥሮ ይመለከታታል። ስልኩ ጮኾ ጭኾ ሲበቃው ዝም ይላል። ትንሽ ሄድ እንዳሉ አሁንም እንደገና ይጮኻል። አሁንም አገላብጣ ብታየው ማንሳት ያቅታታል። አጠገቧ የተቀመጠውን ሰው እንዳትጠይቅ የማይሆን ነገር ነው።

ሰውየ ቢጨንቀው እሱን ስልክ ለምን አታነሺውም ብሎ መጠየቅ ያዘ። መልስ ጠፋ። ድንገት አይኑን ወደ ስልኩ ሲወረውር ስልኩ ላይ የሚያወቀው ሰው ፎቶ ግራፍ ይመለከታል። እኚህ ሴት ዳኛዪቱ አይደሉም እንዴ ይላል። እግዜር ሲፈርድባት ለካ ሰውየው ፖሊስ ነው። ሳያስበው እጁ የገባችን ሲሳይ እያጫወተ ጋሞጎፋ ይደርሳሉ። አገሯ ለመግባት ቆርጣ በመጣችው ትኬት ቤቷ ሳትገባ ፖሊስ ጣቢያ ተረከባት።

ከዚያማ በፖሊስ ታጅባ ጉዞዋ አዲስ አበባ ወደሚገኙት ዳኛ ሆነ። እሳቸው ደግሞ የህግ ሰው ስለሆኑ ክስ መሰረቱባት አሉ። መቸም ህጉም እግዜሩም ዳኛውም በደሀ ይበረታል። ሀብታም ሆና ሚሊዮኑን ብትዘርፍ ኖሮ ሙስና ይባልላት ነበር። አሁን ግን ሌባ ልትባል ነው። ምስኪን!

Page 13: Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 … 92.pdf · Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, ... በቀድሞው

ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ Zethiopia Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com 13

IS Libya killings videos haunts asylum seekers in Israel?

Cops: he was trying to commit suicide(Atlanta ,Giorgia )

Yared Woldemariam of Lawrenceville was arrested by Gwinnett County Sheriff ’s deputies on charges of reckless conduct and reckless driving, in addition to traffic violations, according to police records . He was first treated at Gwinnett

Medical Center for what authorities described as non life-threatening injuries.

No other injuries were reported, though his Toyota 4Runner is said to have struck two

cars in the area of the busy Pleasant Hill Road stoplight where the dramatic wreck began.

It was on the way to the hospital that the suspect allegedly revealed his

plans.

“A Gwinnett County EMT

first responder called to the scene stated during his assessment of the

(SEATTLE) — Yosef Habte and Yemane Bahtta have been charged in connection with a sophisticated skimming ring where detectives said they glued skimming devices on card readers and placed cameras on

ATMs across Seattle.John Incardona said if it weren’t for detectives he would have never known his Chase debit card was skimmed.

“I didn’t really have any knowledge from the bank. I learned from the Kirkland Police Department,” said Incardona.

Kirkland police said that it investigated the case because many of the victims live in Kirkland.

Local officers worked with U.S. Secret Service on the case.

They said Habte and Bahtta are connected to at least 24 skimming incidents from 2012 - 2013.

Detectives believe more victims are out there.

San Francisco police recover stolen car with baby inside

A 4-month-old was back with her family safe and sound after the car she was riding in was stolen last April 29, 2015 in San

Francisco.

“The car was running. Someone kicked the

car. My husband came out of the car to check because he didn’t know if he had hit someone. And that was when

someone got in the car and drove off,” the baby girl’s mother said.

Police officers were flagged down on Golden Gate Avenue at 10:41 and told that a Toyota Scion had been stolen with the child inside. 10 minutes later, an officer spotted the vehicle on 7th Street in front of the Public Defender’s office, recovered the infant and arrested the driver.

The girl’s mother was clearly emotional during the reunion.

“I’m very relieved to

Demeke arrested for attempted murder after Treme street disputeOn May 15,2015 Abiy Demeke was arguing with the victim at the corner as police rolled by. The disagreement continued onto the neutral ground and then Demeke started punching the other man.

As the two troopers parked their vehicle, Demeke fled from the scene. Sgt. Paul Chamorro chased him around an abandoned

building and back onto the street. He fell, hopped back onto his feet, but was apprehended by the other trooper.

Demeke dropped a Smith and Wesson handgun where he fell, according to the report. The victim told officers that Demeke had used the gun both to strike him and to fire off a round while demanding money.

Demeke, 29, has been booked on charges of attempted first-degree murder, attempted armed robbery, resisting an officer, aggravated battery, simple battery, and criminally negligent discharge of a firearm. Judge

Harry Cantrell set Demeke’s bond at $480,000 on Monday.

(theneworleansadvocate)

Amanuel Menghesha, accused of killing a veteran Fulton County police officer in an ambush attack has been indicted on murder charges, the District Attorney told the Atlanta Journal-Constitution

Amanuel Menghesha, 42, of Fairburn, allegedly shot Detective Terence Avery Green in the back of the head in March as several officers responded to a report of shots being fired, according to police. Green, 48, died from his injuries.

A 22-year veteran of the department, Green was killed in the early-morning hours of March 4 as he and six other officers searched for the suspect in The Parks of Cedar Grove subdivision in south Fulton

County, according to police.

Fulton police had been called before to Menghesha�s home in the 7000 block of Parks Trail. In November, he was arrested after allegedly assaulting his daughter

and choking and threatening to kill his fiancée. He was due in court to answer the charges just days before he allegedly killed Green.

Around 1 a.m. March 4, Menghesha allegedly fired several shots at the officers, striking Green and a second officer, who was struck on his duty

belt. The second officer’s radio was destroyed, but Green was gravely injured, and died after being taken to Grady Memorial Hospital. Thousands attended Green’s funeral, including law enforcement officers from across Georgia.

Officers returned fire striking Menghesha, who spent more than two weeks in the hospital before being booked into the Fulton County jail.

The 29-count indictment returned against Menghesha includes charges of murder, felony murder, criminal attempt to commit murder, aggravated assault against a peace officer, reckless conduct, criminal damage to property, violating family violence order and weapons offenses in connection with the shooting death of Green, DA Paul Howard said.

(The Atlanta Journal-Constitution Alexis Stevens)

Mengehsa indicted for killing Fulton County detective

Model’s split from husband finally made public

Liya Kebede who�s having a major moment as the first black model to grace the cover of Paris Vogue in five years, and is a favorite of hot Louis Vuitton designer Nicolas Ghesquière � has quietly separated from her hedge-under husband Kassy Kebede.

Liya, 37 — the Ethiopian-born beauty who has been a World Health Organization goodwill ambassador and has her own clothing line, Lemlem — wed Kebede in 2000. He runs Panton Capital Group and previously helped create Deutsche Bank’s global-markets division.

The couple has two kids. But a source

close to the model tells pagesix, they’ve been separated “for two years — it’s never been written about.”

Eyebrows were raised in Cannes when Jake Gyllenhaal rushed through a crowd to Kebede at the fest’s opening gala. “Jake focused right in on her,” said a spy.

They were talking for a long time. It was very flirty, Jake had her laughing.� But his rep said the pair are just friends through a financier of Gyllenhaal�s hit �Source Code.� Liya was in Cannes for L�Oréal with Julianne Moore and Naomi Watts. (Source Pagesix)

Yared charged after flipping car into Taco Bell patient (he) stated that he was trying to commit suicide,” a Gwinett police officer wrote in a report, “and that was the reason for his reckless conduct and driving.”

Hran the red light at Satellite Boulevard. He reportedly hit a Honda Accord that was turning onto Pleasant Hill and then left the road, struck two business signs, shot into the air and hit another car while flipping. The 4 Runner finally stopped crashed into the front entrance of the Taco Bell, according to the report.

Multiple witnesses came forward to say

Woldemariam hadn’t been driving safely before the wreck. One man, a delivery driver, claimed the suspect had been watching him for some reason while he made a delivery earlier and then sped away “aggressively.”

Woldemariam arrived five and a half hours later at the Gwinnett jail, where he appeared to crack a smile in his mugshot.

He remained held on $11,496 bond Friday. (gwinnettdaily)

Abiy Demeke (New Orleans Police Department)

Today, I have a new Commander-in-Chief – JesusDuring my years in prison, I learned a lot. From an avowed atheist, I turned into a reluctant sceptic and finally emerged as a Christian. Today, I carry the Lord’s word across the world – from Philippines to India, from Dubai to Switzerland and the United Kingdom. Today, I have a new Commander-in-Chief – Jesus — and I go where he orders me to and do what he commands me to. Before moving ahead, Ethiopia must heal the wounds of its past and this can only be done through forgiveness and peace and reconciliation. Our work in the country remains unfinished, we could not achieve what we had set out to achieve and our intentions remain unrealized. So, yes, this is a unique opportunity for redemption, and it may never again come our way. As I have said repeatedly, this is unfinished business. The sooner we complete it, the sooner we will heal and prosper, individually and as a nation.

On his recent visit to India, Tamrat Layne spoke to TEHELKA’s daily, about his chequered life and his hopes of a new future, founded on peace and reconciliation – for both himself and his beloved country.

Incardona said while Chase Bank alerted him that his account was compromised, it did not say that he was skimmed.

“Even the ATMs they have a sign that say protect your pin other than that how do you protect yourself from some invisible skimming devices,” said Incardona.

A spokesperson for Chase said, “When we detect or learn of a skimming situation, we quickly reissue new cards to our affected customers. The customers have zero liability for any fraudulent transactions on their card.”

Detectives say that because skimming devices are becoming more sophisticated it’s up to customers to keep a close eye for anything suspicious.

(By David Ham www.kirotv.com)

reunite with my baby. Before I could find the baby, I was worried. She’s so little, I didn’t know what was going to happen to her,” she said.

The suspect was later identified as 33-year-old, San Francisco resident, Solomon Alemu. Alemu was booked into San Francisco County Jail on charges of vehicle theft, kidnapping and child endangerment charges on top of probation violation. (CBS5)

Tamrat Layne former Prime Minister of Ethiopia

Chase Bank ATMs targeted in sophisticated skimming ring

Page 14: Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 … 92.pdf · Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, ... በቀድሞው

ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ Zethiopia Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com 14

Eritrean asylum seeker: It was horrible. I’ve never seen anything like it in my life.

Illegal migrants can be held for up to 20 months under Israeli law

TEL AVIV - Sitting in his sparsely furnished flat in Tel Aviv, Fikre Mariam lowers his eyes and recounts watching footage of his cousin -- a fellow Eritrean asylum seeker -- beheaded by jihadists in Libya.

“It was horrible. I’ve never seen anything like it in my life,” says Mariam, one of tens of thousands of African migrants who has sought asylum in Israel.

“Those people are not human

አገዛዝ የትግል ዓመታት ንቅናቄያችንን በጋራ ነበር የገነባነው:: ታንዛንያ ውስጥ የጋራ የጦር ካምፕ ነበረን:: የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ ተዋጊ ሃይል (Umkhonto we Sizwe) ካድሬዎች ከአንጎላ የኤም ፒ ኤል ኤ አባላትና ከኩባ ጓዶች ጋር ተሠልፈው ለአንጎላ ነፃነት ተዋግተዋል::

ደቡብ አፍሪካ ከዚህ የትግል አንድነትና ወዳጅነት መንፈስ አልወጣችም:: አልተለወጠችም:: ነገር ግን ከቀውስ አዙሪት እንደወጡ በርካታ ሃገሮች ሁሉ እኛም ከባድ ፈተናዎች አሉብን:: የውጭ ተወላጆች ለደቡብ አፍሪካ የሚያደርጉትን አስተዋፅኦ በውል እንገነዘባለን:: መዋዕለ ንዋያቸውን በማፍሰስና እውቀታቸውን በመጠቀም በእግረመንገድም የምንኮራበትን የዜጎች ስብጥር በመፍጠር ለኢኮኖሚያችን እድገት የጎላ አስተዋፅኦ ያደርጋሉ::

በዚሁ ልክ ታዲያ በዜጎቻችን በኩል የሚነሱና መፍትሄ የሚፈልጉ አንዳንድ ቅሬታዎችና ችግሮችም አሉ:: ከነዚህም መካከል በህገወጥ መንገድ የሚገቡና የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው ሰዎች

መበራከት፣ በአነስተኛ የንግድ መስክ የተሰማሩ በርካታ ሰዎች በውጪ ተወላጆች አማካይነት መፈናቀላቸው፣ የተወሰኑት የውጪ ተወላጆች ደግሞ በህገወጥ መንገድ መንቀሳቀሳቸው፣ … የሚሉት ይገኙበታል:: እነዚሁ የውጪ ተወላጆች በአደንዛዥ እፅ ንግድና በህገወጥ የሰዎች ዝውውርም ይታማሉ:: በአካባቢው ተወላጆች የተያዙ የሥራ መስኮችን ነጥቀው በዝቅተኛ ደመወዝ ለሚሠሩ የውጭ ዜጎች ለመስጠት ከሚፈልጉ ቀጣሪዎች ጋር ይተባበራሉ:: በዚያ ላይ ደግሞ መንግስት የገቢ ምንጭ ለሌላቸው ሰዎች ያዘጋጃቸውን ነፃ የመኖሪያ ቤቶች ተቆጣጥረዋቸዋል የሚል ቅሬታ ይቀርባል:: በበኩላችን ግን እነዚህ ሁሉ ቅሬታዎችም ቢሆኑ ማናቸውንም አይነት የጥቃት እርምጃ በውጪ ተወላጆች ላይ የመውሰድን ተገቢነት እንደማያረጋግጡ ግልፅ አድርገናል::

መንግስት ይህን አይነቱን የአመፃ ተግባር በምንም መንገድ እንደማይታገስም አስታውቋል:: ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ያሉ የውጭ ተወላጆች ሁሉ በህገወጥ መንገድ የሚኖሩ አለመሆናቸውንና በወንጀል ድርጊት

የተሰማሩትም ቢሆኑ ብዙሃኑን እንደማይወክሉ እያስገነዘብን ነው::

በደቡብ አፍሪካውያን በኩል የሚቀርቡ ቅሬታዎችንና የበርካታ ስደተኞችን፣ የፖለቲካ ጥገኝነት ጥያቄ አቅራቢዎችንና ለሥራ ፍለጋ ከአፍሪካም ሆነ ከሌላ አህጉር የሚመጡ ወገኖችን ዕጣ ፈንታ ሚዛናዊ በሆነ መንገድ ማስታረቅ ያስፈልጋል:: ዘላቂ መፍትሄ የሚያመጡ እርምጃዎችን መውሰድም አለብን:: ባለፉት ሳምንታት ከተፈጠሩት ችግሮች ባሻገር እየተመለከትንም ነው::

የስደተኞችን አቀባበልና አስተዳደር ሰፋ ባለ መንገድ አጥንቶ የሚያቀርብ 14 ሚኒስትሮች በአባልነት የሚገኙበት ኮሚቴ እንዲቋቋም አድርጌያለሁ። ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በሚያገኙት ድጋፍም ለዚህ በዜጎችና ከአፍሪካ፣ ከባንግላዴሽና ከፓኪስታን በመጡ ወንድሞችና እህቶች መካከል ለተፈጠረው የማህበረ ኢኮኖሚያዊ ፍጥጫ ሰበብ ለሆኑት ጉዳዮች መፍትሄ ያፈላልጋል። ያን መሰል የአመፅ ተግባር ዳግም የማይከሰትበትን

መንገድ ይፈጥራል። እስካሁንም ከንግዱ ማህበረሰብ፣ ከሠራተኞች፣ ከስፖርተኞች፣ ከሃይማኖት መሪዎች፣ ከወጣቶች፣ ከሴቶች፣ ከህፃናትና ከሌሎችም የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በጉዳዩ ላይ መክረንበታል፣ ዘክረንበታል። መፍትሄ በማፈላለጉ ሂደትም በሃገራችን ኗሪ የሆኑ የውጪ ተወላጆችን ከሚወክሉ ድርጅቶች ጋር እየተመካከርኩ ነው። ሚኒስትሮች፣ አስተዳዳሪዎች፣ ምክትል ሚኒስትሮችና ሌሎችም የመንግስት ባለስልጣናት በመላ ሃገሪቱ ተሰማርተው መልእክታችንን ለደቡብ አፍሪካውያን እያደረሱ ነው። የህዝቡንም አስተያዬት እየተቀበሉ ነው።

የአጭር ጊዜ እቅዳችን ደግሞ የስደተኞች ጉዳይ ፖሊሲያችንን ማሻሻልና የሃገሪቱ ህግ በሚያዘው መሰረት የድንበር ላይ ቁጥጥሩን ጠበቅ ማድረግን ያካትታል። ጎን ለጎንም የውጪ ተወላጆችንና ዜጎችን የወቅቱ የማህበረ ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ የፈጠረውን ውጥረት ተጠቅመው ለወንጀል ተግባር ከሚንቀሳቀሱ ቡድኖች እንጠብቃለን። የሃገሪቱን የስደተኞች ጉዳይ ፖሊሲ ከወቅቱ ሁኔታና በቅርብ ካጋጠሙን

ተሞክሮዎች ጋር አዛምዶ የመመርመሩም ሥራ ተጀምሯል።

መንግስታችን ስደተኞች በብዛት ከሚመጡባቸው እህት ሃገሮች ጋር በመተባበር ለችግሩ መፍትሄ ማግኘት እንደሚቻል በፅኑ ያምናል። ከአፍሪካ ህብረት፣ ከተባበሩት መንግስታትና ከሌሎችም አካባቢዎች የደረሱንን የማበረታቻ መልእክቶች ከአክብሮት ጋር ተቀብለናል። የሰላም ወዳዱ ህዝባችን ሙሉ ድጋፍ ከእኛ ጋር መሆኑም እንደመንግስት የምናደርገውን ጥረት እያጠናከረልን ነው። በመላ ሃገሪቱ እየተካሄዱ ያሉት የሰላምና የወዳጅነት ሰልፎችም የምናውቃትንና የምንኮራባትን ደቡብ አፍሪካ ፍንትው አድርገው እያሳዩ ነው።

ውድ ወንድሜ ሆይ፣ ከዚህ የቁጣና የሃዘን ስሜት ወጥተን፣ ዘላቂና አስተማማኝ የሆነ ልማትን፣ ሰላምና ወዳጅነትን በመላ አፍሪካ ለማስፋፋት በምናደርገው ጥረት ከጎናችን እንድትቆም እጋብዝሃለሁ።

አክባሪህ

ያዕቆብ ዙማ

በእግር ኳስ ስፖርት ዓለም ሰሞኑን መነጋገሪያ ሆኖ የሰነበተው የአርሰናሉ ወጣት ቡድን ተሰላፊ፣ ጌዲዮን ዘለዓለም፣ ለዋናው የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን የሚጫወትበት ጊዜ ሩቅ እንደማይሆን መነገር ጀምሯል። ከኢትዮጵዊ ደም በጀርመን አገር ተወልዶ ሜሪላንድ ያደገው ጌዲዮን ለአሜሪካ ለመጫወት የሚያስችለውን አሜሪካዊ ዜግነትና የፊፋን ህጋዊ ፈቃድ አግኝቷል። ለመጀመሪያ ጊዜም ከ20 ዓመት በታች በሆኑ የዓለም

አቀፍ ወጣቶች እግር ኳስ ውድድር (U-20 World Cup) ላይ አሜሪካን ወክሎ በመሰለፍ የተደነቀ ጥበቡን ማሳየት ጀምሯል። ከስር ከስሩ እየወደለ የሚያነጋግረው የዩናይትድ ስቴትስ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን አሠልጣኝ ጀርመናዊው የርገን ክሊንስማን ጊዲዮን ወደ ዋናው ብሔራዊ ቡድን በመምጣት ተሰልፎ መጫወት የሚችልና ተስፋ የሚጣልበት ድንቅ ተጫወች ነው ማለቱ ተዘግቧል።

በድንቅና ተስፋ ሰጪ ተጫወችነቱ የአርሰናል ክለብ 2017 ድረስ በኮንትራት የያዘው መሆኑ ተወርቷል። ለዋናው የአርሰናል ክለብ ደርሶ መጫወት እስኪችል ድረስ በውሰትም ሆነ በኪራይ ለሌሎች ክለቦች ሄዶ መጫወት የሚችልበትም እድል ሊመቻች መቻሉም እየተነገረ ነው። ጌድዮን ምንም እንኳ ለአርሰናል የፕሪሚዬር ሊግ ጨዋታ እስካሁን ተሰልፎ የተጫወተባቸው አጋጣሚዎችም ባይኖሩም በኤፍካፕ ተጫውቷል። አንድ ሁለት ሶስት

ጊዜም በቋሚ ቡድን ተሰላፊዎች ዝርዝር ውስጥ ለመግባት ችሏል። በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ላይ አርሰናል ከቱርኩ ክለብ ጋር

ባደረገው ጨዋታ ከእረፍት በኋላ ተቀይሮ በመግባት ለመሰለፍ በቅቷል።

የኳስ ዓለም ሰዎች « አዲሱ ሴስክ ፋብሪጋስ » (next Cesc Fabregas) በማለት የሚያሞካሹት ልጅ እግሩ ጌዲዮን፣ ስለወደፊት ተስፋው እንዲህ ሲል ተናግሯል፦

"የአርጀቲናው ሜሲ በ2005 የነበረበትን ደረጃና ውጣ ውረድ ሰው ሁሉ ያስታውሳል። ከዛ ተነስቶ ዛሬ የት ደርሷል። እኔም ዛሬ ያኔ እሱ የነበረበት ደረጃ ላይ እሆን ይሆናል። ለነገዬ የምመኘው ግን የእሱን አርዓያ መከተል ነው።"

በአማካይ ወይም በአከፋፋይ ቦታ

የሚጫወተው ፈጣኑ ጌዲዮን ኳሷን ሲያሽሞነሙናት፣ ዋጥ ፀጥ ሲያደርጋት፣ ለተቀባዮች ፈትፍቶ ሲያጎርሳት የሚደነቅበት ጥበቡ ነው። የእድሜው ለጋነትና ያቺ ኢትዮጵያዊነትም አንድነት ሆነው፣ ሰውነቱን ትንሽ ማፈርጠም እንደሚገባው ሳያስታውሱት አይቀርም። በተረፈ፣ ኢትዮጵያውያን በዓለም አቀፉ ኳስ ሜዳ፣ ተመልካች ብቻ ሳይሆኑ፣ ተጫዋች የሚሆኑበት ቀን እየቀረበ መሆኑን ከሎጋው ጌድዮን ዘላለም፣ ያማረ ተስፋን መሰነቅ ይቻላል።

የአርሰናሉ ጌዲዮን ዘላለም ለአሜሪካ ተስፋ እየሆነ ነው

ጊዲዮን ላይ የወደፊት ተስፋ ከጣሉት መካከል የአርሰናል አሰልጣኝ አርሰን ቬንገር ቀዳሚው ናቸው" zelalem is a creative player and he can create a spark, an opening with his passing, his vision through the lines- " Wenger on Zelalem

በትክክል ፈጽመው? በጤና ጉድለት ታውከው? በሐሰት ተወንጅለው? ወይስ ምን የሚያስደንቅ ነገር አለ?አሜሪካ ውስጥ በርካታ ኢትዮያውያን በየእስር ቤቱ በመማቀቅ ላይ ይገኛሉ። ወንጀለኞች ቢሆኑም በሀሰት ተወንጅለውም ቢሆን ወይም በጤና እክል የተነሳም ቢሆን ሁሉም ውሎ አድሮ ለኮሙዪኒቲው ጉዳት ነው። በዚህ ዙሪያ ያለው እውነታ እንዴት እንደሆነ የሚያውቅ የለም። ስለሱ የሚያወራም በዚህ ዙሪያ የሚሠራም መኖሩን አናውቅም። ጉዳዩ እያደገ መምጣቱ ግን መረጃዎችን እየተመለከትን ነው። እዚህ ለአብነት የተጠቀሱት ባለፉት ሁለት ወራት ብቻ ከተከሰቱት ጥቂቶቹን ብቻ ነው። በዚህ ዙሪያ መረጃዎችና ጠቃሚ አስተያየቶች ካላችሁ ላኩልን።

አትላንታ- አማኑኤል መንገሻ የካውንቲውን ተኩሶ ፖሊስ ገደለባለፈው ሜይ 4/2015 ከፖሊሶች የተታኮሰው የ42 ዓመቱ አማኑኤል መንገሻ ሌሎቹን ቢስታቸውም በ ጆርጂያ አትላናታ የፋልተን የካውንቲ ፖሊስ ኦፊሰር የሆነውን የ48 ዓመቱን ቴረንስ አቨሪ ግሪንን ተኩሶ ገድሏል በሚል የግድያ ወንጀልና ሌሎች ተደራራቢ ክሶች ተመስርተውበት በካውንቲው እስር ቤት ይገኛል። ተከሳሹ ከዚህም በፊት ባለፈው ኖቨምበር ላይ ልጁን ደብድቧል እጮኛውን አንቆ ሊገድል ታጓሏል በሚል ፖሊሲ ተጠርቶበት እንደነበርና ጉዳዩ በፍርድ ቤት በመታየት ላይ እንደነበር ተዘግቧል። እንዲያውም ያሁኑን ግድያ ከመፈጸሙ ጥቂት ቀናት በፊት በዚሁ ጉዳይ ፍርድ ቤት ቀርቦ ቃሉን መስጠት እንደነበረበት ተነግሯል።

ሲያትል - ዮሴፍ ሀብቴና የማነ ባሕታ ኤ.ቲ .ኤም ማሽኖችን በኮድ መንተፈዋል ተብለው ተከሰሱ

በሲያትል ዋሽንግተን የኤቲ ኤም ማሽኖችን ኮድ እያነበበ የሚመነትፍ መሳሪያ በስውር ገጥመው የሰዎችን ዴቢት ካርድ እያነበበ ገንዘብ የሚወስድ መሳሪያ ሠርተው ሲጠቀሙ ኖረዋል በሚል የተጠረጠሩ ሁለት ኤርትራውያን በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተነግሯል።መመንተፊያ መሳሪያዎቹ እጅግ የተራቀቁ መሆናቸውን የባንክ ባለሙያዎችና መርማሪዎች ቢገልጹም ሰዎች ገንዘብ ለማውጣት ወደ ኤቲ ኤም ማሽኖች ሲሄዱ በማሽኖቹ ዙሪያ ያሉትን ነገሮች እንዲቃኙ አስጠንቅቀዋል። የቼዝ ባንክ እንደገለጸው ባንኩ ጥንቃቄ የሚያደርግና ለደንበኞቹ ወዲያውኑ የሚያሳውቅ ሲሆን በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ ገንዘባቸው ለሚሰረቅ ደንበኞች ባንኩ ወዲያ ገንዘቡን እንደሚተካ መግለጻቸው ተዘግቧል። ሌሎችም ባንኮች ተመሳሳዩን እንደሚፈጽሙ የሚታመን ሲሆን፣ ዮሴፍ እና የማነ ከ2012 እስከ 2013 ድረስ ብቻ ቢያንስ 24 ከሚሆኑ ሰዎች ላይ ሳይወስዱ እንዳልቀረ ተገምቷል። እስካሁን የቀረቡት ጥቂቶች ናቸው።

አትላንታ- ራሱን ለማጥፋት ንብረት ያጠፋው ያሬድ ተያዘ

ጁን 11 ከማለዳው ሶስት ሰዓት ተኩል ግድም አትላንታ ውስጥ ቶዮታ ፎር ራነር ኤስ ዩቪ መኪናውን በፍጥነት እያሽከረከረ ድንገት አቅጣጫ ለውጦ ታኮ ቤ ሬስቶርንትን በርቅሶ ለመግባት የሞከረው አቶ ያሬድ ወልደማርያም ክስ ተመስርቶበታል። ያሬድ ድርጊቱን የፈጸመው ራሱን ለመግደል አስቦ እንደሆነ መናገሩን ፖሊስ አስታውቋል። ቋሚ የንግድ ምልክት ምሶሶዎችን ገነጣጥሎ ወደ ሬስቶራንቱ የገሰገሰው መኪና አራት እግሮቹን ሰቅሎ ወደላይ ቢገለበጥም ያሬድ በሰላም መውጣቱና ወደ ሆስፒታል ተልኮ ምንም ጉዳይ ያልደረሰበት መሆኑን ፖሊስ አስታውቋል። ከሆስፒታል በኋላ ወደ እስር ቤት የተወሰደው ያሬድ የ11ሺ496 ብር ዋስ የተጠራበት ሲሆን በአደገኛ አሽከርካሪነትና በትራፊክ ህግ ጥሰት መከሰሱ ተዘግቧል። በአደጋው የተጎዳ ሰው የለም።

ኒው ኦርለንስ - አብይ ደመቀ በመግደል ሙከራ ተከሰሰ

ባለፈው ሜይ 15 በኒው ኦርለንስ አብይ ደመቀ በመግደል ሙከራ፣ በስርቆትና፣ ከፖሊሶች ጋር ግብግብ በመፈጸም ተከሶ ግማሽ ሚሊዮን የሚጠጋ የ480ሺ ዶላር ገንዘብ ዋስ ተጠይቆበት እስር ቤት እንደሚገኝ ተዘግቧል።

በጎዳና ላይ ድብድብ ሲፈጽም በቦታው በመገኘቱ በቦታው የደረሱትን ፖሊሶች አልምልጦ ለመሮጥ ቢሞክርም ተይዞ በቁጥጥር ስር ውሏል የተባለው አብይ ሹጉጥ አውጥቶ በማስፈራራት ተበዳዩን ገንዘብ እንዲሰጠው ማስፈራራቱን ከሳሽ ተናግሯል ሲል የኒው ኦርለንስ ፖሊስ አስታውቋል።

ሳንፍራንሲስኮ- ሰለሞን ዓለሙ የሰው መኪና ነጥቆ በረረ- ከኋላ የ4 ወር አራስ ልጅ ተቀምጣ ነበር

ሜይ ወር ሊገባ አንድ ቀን ሲቀረው፣ ሜይ 29 ሳንፍራንሲስኮ ውስጥ፣ ከኋላ አራስ ጨቅላ ልጁን የጫነ አባት መብራት ላይ ቆሟል። ድንገት ከበስተኋላ አንድ ነገር መኪናውን በኃይል ይደልቀዋል።

ከባድ ድምጽ በመሰማቱ ግራ የተገባው አባት መኪናዬ ምን ተደርጋለች ብሎ ጉዳቷን ሊመለከት ይወርዳል። በዚህ ጊዜ አባት ገና ከኋላ እንደቆመ መኪናዪቱ ፈተልክ ብላ ታመልጣለች። ድንጋጤ ይሆናል። ከሁሉም በላይ ህጻን ልጅ መኪና ውስጥ አለች።

እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን ሁኔታውን የሰሙ ፖሊሶች ተከታትለው መኪናዪቱን ይደርሱባታል። ወይም ሹፌሩ ምን ዓይነት ነገር ነው ባካችሁ አሁን ይሄን የአራት ዓመት ህጻን ልጅ ምን አደርገዋለሁ ብሎም ሊሆን ይችላል። ብቻ በሉ እምታደርጉኝ አድርጉኝ ዓይነት ሆኖ ይቆማል።

ለነገሩ ሰለሞን መጀመሪያውያኑም ቀድሞ በፈጸመው ጥፋት በገደብ ያለ ሰው ሳይሆን አልቀረም። እዚያው ፖሊሶቹ ሠፈር ነው ሄዶ የቆመው። ፖሊሶችም የፍጥኝ አስረው ወደ እስር ቤት ወሰዱት! በመሆኑም እስረኛው የ33 ዓመት ወጣት ሰለሞን አለሙም በመኪና ስርቆት ህጻኒቱን ለአደጋ በማጋለጡና ቀደም ሲል የተጣለበትን ገደብ በመጣሱ ክስ ተመስርቶበታል።

ስደት፣ የጠቢብና ፖለቲከኛ ጭውውት... ከገጽ 12 የዞረ

ወገንና ወንጀል

Page 15: Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 … 92.pdf · Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, ... በቀድሞው

15ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ Zethiopia Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com

Eritrean asylum seeker: It was horrible. I’ve never seen anything like it in my life.

Illegal migrants can be held for up to 20 months under Israeli law

TEL AVIV - Sitting in his sparsely furnished flat in Tel Aviv, Fikre Mariam lowers his eyes and recounts watching footage of his cousin -- a fellow Eritrean asylum seeker -- beheaded by jihadists in Libya.

“It was horrible. I’ve never seen anything like it in my life,” says Mariam, one of tens of thousands of African migrants who has sought asylum in Israel.

“Those people are not human

beings -- it’s pure terrorism to commit and film atrocities like that.”

Mariam’s cousin, 30-year-old Tesfay Kidane, was among a group of at least 28 African Christians killed in the graphic video released on April 19 by the Islamic State group in Libya.

Sixteen of the victims were shot in the head while the rest, including Kidane, were beheaded.

The video said the victims were Ethiopians, but Kidane and two others have since been identified as Eritreans who were reportedly trying to reach Europe by sea through Libya after being rejected

for asylum in Israel.

Their deaths have thrown the spotlight on the Jewish state’s controversial immigration policies, which rights groups say have seen thousands of African asylum seekers coerced into “voluntary” departures.

Kidane’s friends and family only learned of his death after the video surfaced, when relatives and a Tel Aviv-based immigrant assistance group identified him and the other two Eritreans.

“It has given me nightmares,” says Kidsti Ghezie, another cousin living in the same flat in southern Tel Aviv, where the walls are decorated

የሚከራይ ቤት አንድ መኝታ ቤት ቤዝመንት (1 Bedroom, Basement) የራሱ መግቢያና መውጪያ ያለው።

የራሱ ሻወርና ኪችን ያለው

ከጆርጂያ ሜትሮ ስቴሽን ጎንGeorgia Metro Station Washington DC, NW

202- 817-4270 ደውለው ያነጋግሩ

በኮምፒዩተር ቴክኖሎጂ የሞያ ዘርፍ ለመሰማራት የሚሰጥ ትምህርት

የሞንትጎመሪ ኮሌጅ ከፍተኛ ተፈላጊነት ባላቸው የኮምፒዩተር ቴክኖሎጂ ሥራዎች ላይ ለመሰማራት የሚያስችሉ የአጭር ጊዜ ኮርሶችን በተመጣጣኝ ክፍያ ይሠጣል። እነዚህ ኮርሶችም፦

• ቢዝነስ አፕልኬሽንስ

• ኮምፒዩተር ኔትወርኪንግ/ሳይበር ሴኪዩሪቲ

• ኮምፒዩተር ኤይድድ ዲዛይን

• ዲጂታል ግራፊክስ/ፎቶግራፊ

• ፕሮግራሚንግ/ሶፍትዌርዴቨሎፕመንት

• ዳታቤዝ ማኔጅመንት

• ሶሻል ሚዲያ/ኔትወርኪንግ

• ዌብ ዴቨሎፕመንት

• እና ሌሎችም

ተጨማሪ መረጃዎችን እና በአማርኛ ቋንቋ እርዳታ ማግኘት ከፈለጉ እባክዎን በኢሜይል አድራሻ [email protected] ወይም በስ.ቁ. 240-777-8478 ሃምራዊት ተስፋን ያነጋግሩ።

የሞንትጎመሪ ኮሌጅ ለሁሉም እኩል ዕድልን የሚሰጥ የትምህርት ተቋም ነው።

ኢሜይል፡ montgomerycollege.edu ስልክ፡ 240-567-5000

Amassive weight has been lifted from Boeing’s

787 Dreamliner inventory and transferred to

Ethiopian Airlines as the carrier

agreed to terms to acquire six of

the “terrible teens” aircraft, ultimately bringing its fleet

to 19.These planes were early line numbers (hence the “teens” part of the moniker) and were some of the most significantly affected by rework efforts as flaws and shortcomings were found in the initial designs (hence the “terrible”). They have been parked at Paine Field outside the assembly line awaiting a customer for nearly five years now.

For Ethiopian Airlines, the 787 is a true game changer. Its hub at Addis Ababa sits at 7600 feet above sea level, making the increased performance of the 787 critical to meeting international growth plans for the carrier. North American routes have had the Rome tech stop removed, service to South America has been added and expansion further into

Asia has been possible. And, while these Terrible Teens planes are heavier than later deliveries, to the tune of an estimated 1000 nautical mile-range penalty, they should still fit well within the carrier’s growth and modernization plans.

Tewolde GebreMariam, CEO of Ethiopian Airlines, spoke to the benefits the Dreamliner brings to the fleet, “This new addition to our fleet will not only benefit

Ethiopian because of its unmatched operating costs, but will also help us to enhance overall travel experience of our customers,” he said.

It is possible that this subfleet may be limited from the longest routes because of the weight penalty and high altitude, but the carrier appears OK with that potential limitation right now. Also, by choosing these planes, delivery can happen much more quickly. And Ethiopian wants the planes quickly even though they are less efficient; adding “regular” 787s today would likely require waiting until the end of the decade or beyond for delivery slots.

And, for Boeing, unloading these aircraft is a milestone moment. They have remained a visible reminder of the early troubles the Dreamliner had and the challenges it has faced in getting to overall profitability for the line. Which is not to say that selling these aircraft has solved those problems, but at least now they will no longer be a visible reminder alongside the flight line in Everett. (By Seth Miller,)

Ethiopian Takes `Terrible Teens’ 787s from Boeing

Early build 787s, dubbed the Terrible Teens, sit unused on a runway outside Boeing’s Everett factory in Washington State. Image: Courtesy of Jeremy Dwyer-Lindgren

/ Special to Airways News

Page 16: Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 … 92.pdf · Zethiopia, Ethiopian American Community News NO.92 July 2015 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, ... በቀድሞው