readmore

46
መ መ መ መ መመመመ መመ መመመመ መመመመመመመ መመመመ መመ መመመመ መመመመመ መመመመመ መመመመመመ መመመመመ መመመመመ መመመ መመመመመመመ መመመመ መመመመመ መመ መመ መመመመ መመመመመመመ መመመመመመ መመመመመ መመመመመ መመመመመመ መመመመመመ መመመመ መመመመመመ መመ መመመመመመ መመመ መመመመ መመመመመመመ መመመመመመመ መመመ መመመመ መመመመ መመመመመመ መመመመመመመመመ መመመ መመመመ መመመመመመመ መመመመመ መመመ መመመመ መመመመ መመመመ /መመመመ መመመ መመመ መመመመመመ መመመመመመመመ መመመመ መመመመመመ መመመመመመመ መመመ መመመመ መመመ መመመ መመመመ መመመ መመመ መመመመመመ መመመመመ መመመመመ መ/መመመ መመመመመመመ መመመ መመመመ መመመመመመ መመመመመመመመመ መመመ መመ መመመመመ መመመመመ መመመመመ መመመመመ መመመ መመመመ መመመመ መመመ መመመመ መመመ መመመ መመመመመመ መመመመመ መመመመ መመመመመመ መመመመመመ መመመመመመመመመ መመመ መመ መመመ መመመ መመመመ መመመ መመመ መመመመመመ መመመመ መመመ መመመመ መመ መመመመ መመመመ መመመ መመ መመመመ መመመመመ መመመመ 1

Upload: vuongduong

Post on 31-Dec-2016

254 views

Category:

Documents


13 download

TRANSCRIPT

Page 1: ReadMore

መ ግ ቢ ያ

የአማራ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት በክልሉ ያሉ የልማት ኃይሎችን በተለይም የመንግስት አካላትን የመፈፀም አቅም የመገንባትና በክልሉ የተጀመሩ ልዩ ልዩ የለውጥ ኘሮግራሞችን የማስቀጠል ኃላፊነት የተሰጠው የስልጠና፣ የምርምርና

ማማከር አገልግሎት ሰጪ መንግስታዊ ተቋም ነው፡፡ ኢንስቲትዩቱ በተጠናቀቀው ዓመት በተለይ ክልላዊ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዝግጅቱ እንዲጠናቀቅ ለማድረግ ድጋፍ ሲሰጥና የክልሉ ሴክተር መ/ ቤቶችም ውጤት ተኮር

ዕቅዳቸውን እንዲያጠናቅቁ ሲደግፍ ቆይቷል፡፡

በተጠናቀቀው ዓመት በክልሉ ውጤት ተኮር ሥርዓት አንድ ርምጃ እንዲራመድ ለማድረግ የሴክተር መ/ ቤቶች የየራሳቸውን ዕቅድ ከክልሉ የዕድገትና ትራንስፎርሜሸን ዕቅድ ጋር አጣጥመው እንዲሰሩ ለማድረግ ከተሰጠው ድጋፍ ባሻገር በክልል ደረጃ የውጤት ተኮር ዕቅድ አዘገጃጀት ሥርዓትን ተከትሎ የተዘጋጀው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ወደ ዞንና ወረዳ

ከውጤት ተኮር ዕቅድ አዘገጃጀት የንድፈ ሃሣብ ስልጠና ጋር ተያይዞ መውረዱ ትልቅ ሥራ ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡

ከላይ ከተጠቀሰው ተግባር በተጨማሪ ኢንስቲትዩቱ ከባህር ዳር ዩኒቪርስቲ ጋር በመቀናጀት ከክልሉ ተመለምለው ለገቡ 64 ያህል (4 ቱ በተለያየ ምክንያት አቋርጠዋል) የድህረ ምረቃ ተማሪዎች ስልጠና የሚሰጥበት ማዕከል ሆኖ ሥራው

እንዲካሄድ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ተጠቃሽ ተግባር ነው፡፡

በአጠቃላይ ኢንስቲትዩቱ በተጠናቀቀው ዓመት የተለያዩ ተልዕኮዎችን በመውሰድ ሲፈፅም የቆየ ሲሆን ከዕቅድ አኳያ የተከናወኑ ተግባራት እና ከዕቅድ ውጭ ሊከናወኑ ይገባቸው የነበሩ ሥራዎች አፈፃፀም በዚህ ሪፖርት ውስጥ ተካተው

ቀርበዋል፡፡

1. የኢንስትዩቱ ተልዕኮ፣ ራዕይና እሴቶች

ተልዕኮ

የክልሉን የልማት ኃይሎች አቅም ለመገንባት ጥራትና ብቃት ያለው በፍላጎት ላይ የተመሠረተ ስልጠና፣ ጥናት፣ ምርምር እና የምክር አገልግሎት በመስጠት ለዘላቂ ልማትና መልካም አስተዳደር መስፈን አስተዋፅኦ ማድረግ፡፡

ራዕይ 2012

ኢንስቲትዩቱ በሥራ አመራር መስክ ብቃት ያለው የለውጥ አስቀጣይ ማዕከል ሆኖ ማየት፡፡

ዕሴቶች

1

Page 2: ReadMore

ኢንስቲትዩቱን የለውጥ አስቀጣይ ተቋም ማድረግ የያንዳንዳችን ኃላፊነት ነው! የአገልግሎታችን ተጠቃሚዎች የህልውናችን መሰረቶች ናቸው! የውጤታችን መለኪያ የተገልጋይ ዕርካታ ነው! መማማርና መተራረም ቁልፍ የሥራ መሣሪያችን ነው! ዓላማችን ሊሰሩበትና ሊገለገሉበት የሚመርጡት ተቋም በጋራ መገንባት ነው!

የ2 ዐዐ3 ዓ. ም ዕቅድ አንኳር መነሻዎች

ኢንስቲትዩቱ የተቋቋመበት ዋነኛ ተልዕኮ የክልሉን መንግስት የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የሚያግዙ ሥልጠና፣ የምክር እና የምርምር አገልግሎት መስጠት ነው፡፡ ኢንስቲትዩቱ በተለይም ከለውጥ

አስቀጣይ ተቋማት መካከል ግንባር ቀደም እንደመሆኑ መጠን አዳዲስ አስተሳሰቦችና የአሠራር ሥርዓቶችን ቀድሞ በመገንዘብ ለቀሪ የመንግስት ተቋማት በማዳረስ የመፈፀም ብቃታቸዉ የጎለበተ ተቋማት እንዲበራከቱ መስራት

ይጠበቅበታል፡፡

በዚህም መሠረት ኢንስቲትዩቱ በ 2003 ዓ. ም ስልጠናን በተመለከተ በውጤት ተኮር ስርዓት (BSC) ርዕስ ለ 810 ሰልጣኞች፣ በቡድን ግንባታና ማብቃት ርዕሶች ለ 1134 ሰልጣኞች፣ በቢሮ አስተዳደርና ሪከርድ ስራ አመራር 5 ዐዐ ሰልጣኞች ስልጠና መስጠት እና የአሰልጣኞችንና አማካሪዎችን አቅም ለማሳደግ የሚያስችል ልዩ ልዩ ስልጠና ለመስጠት አቅዶ ነበር፡፡ የሚሰጡ ስልጠናዎችም ከወቅቱ ተጨባጭ ሁኔታና ከደረስንበት ደረጃ ጋር የተጣጣሙ እንዲሆኑ

የስልጠና ሞጁል የማሻሻል ስራ የዕለት ከዕለት ስራ መሆን ያለበት በመሆኑ በበጀቱ ዓመቱ የስልጠና ሞጁል ማሻሻልም ትኩረት የተሰጠው ዕቅድ ነበር፡፡

ከምክር አገልግሎት አኳያ በለውጥ ኘሮግራሞችና በተዛማጅ የስራ አመራር ጉዳዮች ዙሪያ የምክር አገልግሎት ፈላጊ ተቋማትንና ግለሰብን ፍላጐት መሰረት ያደረገ የምክር አገልግሎት በመስጠት ለውጡን የመደገፍ ዕቅድ ተይዟል፡፡

በዚህም በክልሉ ለሚገኙ 14 ቢሮዎች እና 2 የልማት ድርጅቶች የምክር አገልግሎት ድጋፍ በውጤት ተኮር ዕቅድ አዘገጃጀትና በመሠረታዊ ሂደት ለውጥ አተገባበር የመስጠት ዕቅድ ተይዞ ነበር፡፡

ከጥናትና ምርምር ስራ አንፃር ተግባራዊ እየተደረጉ ባሉ የስራ አመራር ስራዎች ዙሪያ ያጋጠሙ ችግሮችን ለመለየትና መፍትሄ ለመጠቆም እንዲሁም ለምክር አገልግሎት አሰጣጥ አጋዥ የሆነ ግብዓት ለማግኘት ተገቢ ርዕስ መርጦ

ወደተግባር መግባት ሌላው የኢንስቲትዩቱ ዕቅድ ነበር፡፡ በተመሳሳይ በሰው ኃይል አመራር፣ በግዥ ፋይናንስና ንብ/ አስተዳደር፣ በስልጠና ድጋፍ አገ/ ትና በአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ ዙሪያ የተለያዩ ዕቅዶች በመያዝ ወደስራ ተገብቷል፡፡

2. የ2003 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃጸም

2.1. የስልጠና፣ ምክር እና የምርምር አገልግሎት

2

Page 3: ReadMore

የኢንስቲትዩቱን ተልዕኮ ከመፈፀም አኳያ በተለያዩ የለውጥ ኘሮግራሞች ላይ ስልጠና መስጠት፣ ከውጤት ተኮር ሥርዓት ግንባታ ጋር በተያያዘ የክልሉ መ/ ቤቶችን መደገፍ እንዲሁም በኢንስቲትዩቱ ውስጥ ለሚሰጡ ሥልጠናዎች የሚሆኑ ማሰልጠኛ ሞጁል መቅረፅና ያሉትንም ማሻሻል ዋና ዋና ዕቅዶች ነበሩ፡፡ በዚሁ መሠረት በተጠናቀቀው

ዓመት ትኩረት ተሰጥቶ የተሰራባቸው መስኮች የክልሉን መንግስት ውጤት ተኮር ዕቅድ ዝግጅት መደገፍና በቢሮ ደረጃ የሚካሄዱ መሰል ተግባራትንም በማገዝ የተለያዩ ስራዎች ተሰርቷል፡፡ ከዚህ ጐን ለጐን በተለያዩ የለውጥ

ኘሮግራሞች ላይ ሥልጠና የመስጠት ሥራዎችም ተከናውነዋል፡፡

ሀ/ የሥልጠና ሥራዎች

ኢንስቲትዩቱ የተለያዩ ክልላዊ የለውጥ ኘሮግራሞችን ለማስረፅ ሥልጠናዎች መስጠት እንደ አንድ ዋና መሣሪያ ይጠቀማል፡፡ በጀት ዓመቱ ከስልጠና አኳያ የተገልጋዮችን ፍላጎት ከመንግስት የትኩረት አቅጣጫዎች ጋር በማዛመድ

ስልጠና ሲሰጥ ቆይቷል፡፡

በውጤት ተኮር ሥርዓት ላይ፣

ከክልሉ ሲቪል ሰርቪስና ከተለያዩ ቢሮዎች ባለሙያዎችን በአጋዥ አሠልጣኝነት በመመልመል ለ 146 ዐ የዞንና የወረዳ አመራሮችና ባለሙያዎች የ 1 ዐ ቀናት የአሠልጣኞች ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ ስልጠናው ለ 6 ቀናት የውጤት

ተኮር ዕቅድ አዘገጃጀት የንድፈ ሃሣብ ስልጠናና ለ 4 ቀናት ደግሞ ይህንኑ የአስተቃቀድ ዘዴ በመጠቀም የተዘጋጀው የክልሉ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ላይ ያተኮረ ነበር፡፡ በተቋማት ጥያቄ መሰረትም በውጤት ተኮር ስርዓት /

BSC/ ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ላይ በክልሉ በተለያየ ደረጃ ለሚገኙ አመራሮችና ባለሙያዎች በድምሩ 523 ወ 406 ሴ 117 ተሳታፊዎች ስልጠና ተሰጥቷቸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የሥራና ከተማ ልማት ኢንዱስትሪ

ልማት ቢሮ ያዘጋጁትን ውጤት ተኮር ዕቅድ ለሠራተኛ በሚያቀርቡበት ጊዜ ለ 327 ሠራተኞች በተለያየ ጊዜ የአንድ ቀን የማስተዋወቂያ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ለገጠር መንገዶች ባለስልጣን የውጤት ተኮር

ስርዓት /BSC/ ዕቅድ ዝግጅት ቴክኒክ ኮሚቴ 19 ( ወንድ 17 ሴት 2) በዕቅዱ ዝግጅትና ትግበራ የአንድ ቀን ግንዛቤ መፍጠር ስራ ተሰርቷል፡፡

በጠቅላላው ለ 81 ዐ ሰልጣኞች ስልጠና ለመስጠት ዕቅድ ተይዞ በውጤት ተኮር ዕቀድ ዝግጅት ስልጠና ለ 2754 ( ወ 1035 ሴ 259) ሰልጣኞች ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

በዚህ የተጠናከረ ድጋፍም የለውጥ ኘሮግራሙ ዋና አካል በሆነው በውጤት ተኮር ምዘና መሠረት ተቋማት ዕቅዶቻቸውን ማዘጋጀትና ለፈጻሚም ማውረድ የሚያስችል አቅም ሊፈጠርላቸው ችሏል፡፡

በሌሎች ርዕሶች ላይ የተሰጡ ሥልጠናዎች

ከርዕሰ መስተዳድር ጽ/ ቤት፣ ዋና ኦዲተር፣ ስነ- ምግባርና ፀረ- ሙስና ኮሚሽን፣ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩትና የአማራ ገጠር መንገዶች ባለስልጣን ለተወጣጡ 31 (3 ሴትና 28 ወንድ) ባለሙያዎች በ Transformational

Leadership and coaching ላይ ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በፕሮጀክት ሥራ አመራር 46 ( ወ 38 ሴ 8) ፣ በ Leadership 41 ( ወ 33 ሴ 8) ፣ በለውጥ ሥራ አመራር 43 ( ወ 36 ሴ 7) ፣ Team

3

Page 4: ReadMore

Building 41 ( ወ 34 ሴ 7) ፣ የጽህፈትና የቢሮ አስ/ ር ሪከርድር ማኔጅመንት 91 ( ወ 3 ሴ 88) ፣ ኦዲት ማኑዋል ላይ 17 ( ወ 13 ሴ 4) ፣ በአጠቃላይ በድምሩ 802 ( ወ 563 ሴ 239) ሠራተኞች በኢንስቲትዩቱ

አማካኝነት እንዲሰለጥኑ ተደርጓል፡፡

በኢንስቲትዩቱ ለ 153 ሠልጣኞች የአገልግሎት አሰጣጥ ሥልጠና ለመስጠት ከታቀደ በኃላ በክልሉ ባህልና ቱሪዝም አነሳሽነት በባህር ዳር ከተማ ላሉ የግል አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ባለቤቶች፣ ሥራ አስኪያጆችና ተቀጣሪ

ሠራተኞች በስፋት በተሰጠው ያገልግሎት አሰጣጥ ስልጠና ብር 132,ዐዐዐ. ዐዐ ከፍሎ ስፖንሰር በማድረግ ለበርካታ የከተማዋ ዜጎች ስልጠና እንዲሰጥ ማድረግ ተችሏል፡፡

ከበጀት ዓመቱ ዕቅድ አኳያ ለ 5 ዐዐ አዲስ ተቀጣሪ ሠራተኞች በመንግስት ፖሊሲዎችና ስትራቴጅዎች፣ ለ 5 ዐ ሠልጣኞች በ TQM ፣ ለ 75 ሠልጣኞች በሥራ ፈጠራ /Entrepreneurship/ እንዲሁም ለ 153 ሠልጣኞች

በሰው ኃይል ሥራ አመራር ስልጠና መስጠት ታቅዶ ሳይከናወኑ የቀሩ ናቸው፡፡

የ አማካሪዎችንና ባለሙያዎችን አቅም ለማሳደግ የተሰጡ ስልጠናዎች

በዓመቱ የተያዘው ሌላ የሥልጠና ተግባር የኢንስቲትዩቱን ባለሙያዎች ብቃት በስልጠና ማሻሻል የነበረ ሲሆን፣ 19 የኢንሰቲትዩቱ ባለሙያችን በማማከር ዘዴ (Consulting) ፣ በCoaching and mentoring ፣ በResearch

and Module Development ፣ በ Advanced Computer Training ፣ በ Transformational Leadership 10 ባለሙያዎች በ TOT ፣ 2 ባለሙያዎች በM&E እንዲሁም 2 ባለሙያዎች በ Financial Management ስልጠና እንዲያገኙ ለማድረግ ታቅዶ ከሌሎች ስልጠና ፈላጊዎች ጋር ተደምሮ በድምሩ 634 ( ወንድ 372 ሴት 262) የማሰልጠን ስራ ተከናውኗል፡፡

በአጠቃላይ የሥልጠና አገልግሎት በአሃዝ ደረጃ ሲታይ የታቀደው 27 ዐ 9 ያህል ሠልጣኞች ማሰልጠን የነበረ ሲሆን በአገልግሎት አሰጣጥ ከተሰጠው ስልጠና ውጭ ኢንስቲትዩቱ ለ 3388 አመራርና ባለሙያዎች ከ 1 ቀን እስከ 1 ዐ ቀናት የሚፈጅ ሥልጠና በኢንስቲትዩቱ ውስጥና ከኢንስቲትዩቱ ውጭ ሰጥቷል፡፡ ይህም ጥቅል

አፈፃፀሙን 125% ያደርገዋል፡፡ ሆኖም የሥልጠና ተግባራቱ በዕቅድ ተመርተው ብቻ የመጡ ባለመሆኑ በቀጣይ ዕቅዱን ከነባራዊ ሁኔታ አኳያ ገምግሞ በመከለስ መፈፀም ትኩረት የሚሰጠው ተግባር ይሆናል፡፡

ለ/ የማማከር አገልግሎት

የለውጥ ሥራዎች እንዲሰርፁ ከሚደረግበት አገልግሎቶች አንዱ በኢንስቲትዩቱ የሚሰጠው የማማከር አገልግሎት ሲሆን ከዚህ አኳያ የዓመቱ ቁልፍ ዕቅድ የክልሉ መንግስትና በሥሩ ያሉ ተቋማት ውጤት ተኮር ዕቅድ ሥራ

እንዲጠናቀቅ ድጋፍ መስጠት ነበር፡፡ በዚሁ መሠረት፡-

የክልሉ ዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዝግጅቱን ከአንድ እስከ ስድስት የሚደርሱ የኢንስቲትዩቱ ባለሙያዎች እየተመደቡ አብረው እንዲሰሩ ተደርጓል፡፡

የክልሉ የተለያዩ ቢሮዎች የውጤት ተኮር ዕቅድ ዝግጅትን በሚደረግ ጥሪ መሠረት የመደገፍ ሥራ ተከናውኗል፡፡

4

Page 5: ReadMore

የአማራ አቀፍ ልማት ማህበር የመሠረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ ጥናቱን ሁለት ባለሙያዎች እየደገፉ እንዲጠናቀቅ ማድረግ ተችሏል፡፡

ጥረት የጀመረው የውጤት ተኮር ዕቅድ ዝግጅትን ሁለት ባለሙያዎች በመመደብ ድጋፍ የተሰጠ ሲሆን በተለያዩ ሁለት ደረጃዎች ላይ ከደጋፊ ባለሙያዎቹ ተጨማሪ የሰው ኃይል በመመደብ የመገምገምና ግብዓት የመስጠት ሥራ ተከናውኗል፡፡

የውጤት ተኮር ዕቅድ አዘገጃጀት አዲስ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ከየቢሮዎች ለሚነሱ የማብራሪያ ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቷል፡፡

የGTZ የዘላቂ መሬት አስተዳደርና ልማት ኘሮጀክት ባ/ ዳር ጋር በተደረገ ስምምነት መሠረት ኘሮጀክት ሥራ አመራርና በ Leadership ላይ ኘሮጀክቱ ላቀፋቸው ወረዳ አመራሮች ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

SWHISA ድጋፍ በሚሰጥባቸው ቢሮዎችና ወረዳዎች ላይ የተሰራውን የሥልጠና ፍላጎት የዳሰሣ ጥናት መሠረት በማድረግ የተዘጋጀው ስልጠና ተካሂዷል፡፡

ዳሽን ቢራ ፋብሪካ አክሲዮን ማህበር ጋር በውጤት ተኮር ስርዓት /BSC/ ዝግጅትና ትግበራ የማማከር አገልግሎት ለመስጠት ውል በመያዝ ባለሙያዎች /አማካሪ/ ተመድቦ እየተሰራ ይገኛል፡፡

በአጠቃላይ ለ 14 ቢሮዎችና ለ 2 የልማት ድርጅቶች የምክር አገልግሎት ድጋፍ ለመስጠት ታቅዶ ለ 15 ቢሮዎችና ለ 3 የልማት ድርጅቶች በመሠረታዊ የስራ ሂደት ለውጥ ጥናትና በውጤት ተኮር ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ዙሪያ የማማከር ድጋፍ ተደርጓል፡፡

ሐ/ የጥናትና ምርምር ሥራ

ይህ ተግባር ከኢንስቲትዩቱ ተልዕኮዎች አንዱ ሲሆን እስከዚህ ዓመት ድረስ በተሟላ መንገድ ያልተጀመረ ስራ የነበረ ነው፡፡ ሆኖም በዚህ አመት በከተሞች አስተዳደር አገልግሎት አሰጣጥ በተለይም በመሬት ልማት

አስተዳደር ዙሪያ ያሉ ችግሮችና መንስኤዎቻቸውን በመለየት የመፍትሄ አቅጣጫ ለማመላከት ከኢንዱስትሪ ስራና ከተማ ልማት ቢሮ ሙያዊ አስተያየት በማካተት ጥናት ለማካሄድ ኢንስቲትዩቱ TOR

እና የጥናት ዕቅድ አዘጋጅቶ መረጃ ለማሰባሰብ ባለሙያዎችን ወደተመረጡ ከተሞች / ጐንደር፣ ደሴ፣ ባህር ዳር፣ ደብረ ታቦር፣ ከሚሴ እንጅባራ እና ደብረ ማርቆስ/ ልኳል፡፡ ይህም በኢንስቲትዩቱ ተልዕኮን

በተሟላ መልኩ ለመወጣት የሚደረገው ጥረት ማሳያ ሊሆን የሚችል ተግባር ነው፡፡

መ/ የሥልጠና ሞጁል ክለሣና ቀረፃ

በበጀት ዓመቱ በኢንስቲትዩቱ ያሉ ማሰልጠኛ ሞጁሎችን ከተደረሰበት የለውጥ ደረጃ አኳያ በመገምገም የሚሻሻሉትን ማሻሻል፣ የሚወገዱትን ማስወገድና በአዲስ መልኩ አስፈላጊ የሆኑትን ለይቶ በቅደም ተከተል

ማዘጋጀት የሚል ዕቅድ ተይዞ ነበር፡፡ በዚሁ መሠረት ከኢንስቲትዩቱ ውጭ ባለሙያዎችን በመጋበዝ ጭምር ሙሉ ግምገማ የተጠናቀቀላቸው ሪከርድ ማኔጅመንት፣ ኢንተርኘርነርሽኘ ሲሆኑ የመጨረሻ ግምገማ የሚጠብቁት

ደግሞ ፡-

5

Page 6: ReadMore

የሰው ኃይል ስራ አመራር አስተዳደር፣ Coaching and Mentoring እንዲሁም የአገልግሎት አሰጣጥ ናቸው፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘም የስልጣኞች ኘሮፋይል፣ የተዘጋጁ ሞጁሎች መረጃ በሶፍትና ሃርድ ኮፒ ተደራጅቶ እንዲያዝ ተደርጓል፡፡

በበጀት ዓመቱ ከሥልጠና፣ ምክርና ምርምር አኳያ የተያዙ ዕቅዶቻችን በተሟላ ሁኔታ ተተግብረዋል ለማለት ባይቻልም ካለፋት ዓመታት አኳያ ግን ተልዕኮ ላይ የማተኮር ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ ለዕቅዱ በተሟላ ሁኔታ

አለመተግበር ዋናው ምክንያት የክልሉ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዝግጅት በርካታ ባለሙያና የተቋሙን ኃላፊዎች ሰፊ ጊዜ መውሰዱ ተጠቃሽ ምክንያት ሲሆን ይህንኑ ተከትሎ የመጣው ዕቅዱንና የአስተቃቀድ

ዘዴውን ያካተተው የ 1 ዐ ቀናት ሥልጠና ከቅድመ ዝግጅት እስከ ድህረ ስልጠና ግምገማና ሪፖርት የወሰደው ጊዜም ቀላል አልነበረም፡፡

ሌላው የሥልጠና ዕቅዶቻችን በተሟላ አግባብ ያልተሳኩበት ምክንያት የክልል ቢሮዎችና ተቋማት ለሥልጠና ሰው በመላክና የላኩትን ሠልጣኝ ወጭ በመሸፈን ረገድ ያለባቸው እጥረት ነው፡፡ ሥራው ወጪ የሚጠይቅ

እንደመሆኑ መጠን ወጪያቸውን እየሸፈኑ የሚያሰለጥኑ መ/ ቤቶች ገና አልተበራከቱም፡፡ ከዚህ በተጨማሪም እንደ አዲስ ተቀጣሪዎችን በመንግስት ፖሊሲና ስትራቴጅ ላይ ማሰልጠን ያሉ ተግባራት ከኢንስቲትዩቱ ቁጥጥር ውጭ በመሆናቸው ለአፈፃፀሙ አለመሣካት አስተዋፅኦ አበርክቷል፡፡

2.2 የግዥ፣ የፋይናንስና ንብረት አስተዳደር

የግዥ፣ የፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ሥራዎች በአንድ ደጋፊ የሥራ ሂደት ውስጥ ተሰባስበው የታቀፉ ተግባራት ሲሆኑ የኢንስቲትዩቱን ተልዕኮ በመፈፀም ረገድ ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ፡፡ በዚህ ዘርፍ ሥር የመደበኛና ካፒታል፤

የውስጥ ገቢ፤ የድህረ ምረቃ፣ የግዥ፣ የንብረት አስተዳደር፣ የግቢና ቢሮ ውበት/አትክልተኛ/ ፣ የፅዳት፣ የገንዘብ ያዥ፣ የጥበቃ፣ የፅህፈትና የቢሮ አስተዳደርና የስምሪት ሥራዎች ይከናወናሉ፡፡ በዚህ ክፍል ከበጀት ዓመቱ ዕቅድ አኳያ ለውስጥና ለውጭ ደንበኞች አገልግሎት የሚውሉ ዕቃዎችን ለማቅረብ እንዲቻል የቀጥታ፣ የውስንና የግልፅ ጨረታ

ግዥ ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡ በፋይናንስ አስተዳደር ስራውም የኢንስቲትዩቱ መደበኛ ወጭዎችን ከማስተናገድ ባሻገር የውስጥ ገቢውን በወቅቱ ለመሰብሰብ ጥረት ተደርጓል፡፡ ይሁን እንጅ መሰብሰብ ያልተቻለ የተወሰነ ገንዘብ ያለ ሲሆን

ይህም ውሳኔ እንዲሰጥበት ለኢንስቲትዩቱ ቦርድ ቀርቦ ውሳኔ እየጠበቀ ይገኛል፡፡

በበጀት ዓመቱ ለመደበኛ ሥራዎች ብር 2,453,007/ ሁለት ሚሊዮን አራት መቶ ሃምሳ ሶስት ሺህ ሰባት ብር ብቻ/ የተመደበ ሲሆን ከዚህ ዉስጥ ለደመወዝ 1,100,000 / አንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሺህ ብር ብቻ/ ተመድቦ የተከፈለው 1,384,636.76 / አንድ ሚሊዮን ሶስት መቶ ሰማኒያ አራት ብር ከሰባ ስድስት ሳንቲም ብቻ/ ነዉ፡፡

ይህም ከተመደበዉ በጀት በላይ ብር 284,636.76/ ሁለት መቶ ሰማኒያ አራት ሽህ ስድስት መቶ ሰላሳ ስድስት ብር ከሰባ ስድስት ሣንቲም ብቻ/ ብልጫ ያለዉ ሲሆን ይህም የሆነበት ምክንያት አገራዊ የደመወዝ ጭማሪ

በመደረጉ ነዉ፣ በበጀት ዓመቱ ለስራ ማስኬጃ የተመደበዉ ብር 1,344,207.00/ አንድ ሚሊዮን ሶስት መቶ አርባ

6

Page 7: ReadMore

አራት ሺህ ሁለት መቶ ሰባት ብር ብቻ/ ሲሆን ከዚህ ዉስጥ ብር 1,343,533.65/ አንድ ሚሊዮን ሶስት መቶ አርባ ሶስት ሺህ አምስት መቶ ሰላሳ ሶስት ብር ከስልሳ አምስት ሳንቲም/99.94%/ በጥቅም ላይ ውሏል፡፡

ለ ካፒታል ስራዎች የተመደበዉ በጀት ብር 10,573,000.00/ አስር ሚሊዮን አምስት መቶ ሰባ ሶስት ሺህ ብር ብቻ/ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ብር 7,000,000.00/ ሰባት ሚሊዮን ብር/ ለግንባታ ሥራ የተመደበ ነው፡፡

ከተመደበዉ የህንፃ ግንባታ በጀት ላይ እስከአሁን ድረስ ብር 7,922,464.4 / ሰባት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሃያ ሁለት ሺህ አራት መቶ ስልሳ አራት ብር ከአርባ ሳንቲም ብቻ/1.13%/ ወጭ ሆኖ የተከፈለ ሲሆን ከተመደበዉ በጀት በላይ ብር 922,464.4/ ዘጠኝ መቶ ሃያ ሁለት ሺህ አራት መቶ ስልሳ አራት ብር ከአርባ ሳንቲም ብቻ/

በመብለጥ ተከፍሏል፡፡ ከዚሁ ግንባታ ጋር በተያያዘ ብር 3,000,000.00 / ሶስት ሚሊዮን ብር/ ለፈርኒቸር ግዥ የተመደበ ቢሆንም እስካሁን ድረስ ክፍያ አልተፈጸመም፡፡ በበጀት ዓመቱ ብር 299,700.00/ ሁለት መቶ ዘጠና

ዘጠኝ ሺህ ሰባት መቶ ብር ብቻ/ ለፈርኒቸር ግዥ አማካሪ የተመደበ ሲሆን ከዚህ ዉስጥ ብር 53,539.79/ሃምሳ ሶስት ሺህ አምስት መቶ ሰላሳ ዘጠኝ ብር ከሰባ ዘጠኝ ሳንቲም/24%/ ወጭ ሆኖ ተከፍሏል፡፡ ብር

273,300.00/ ሁለት መቶ ሰባ ሶስት ሺህ ሶስት መቶ ብር ብቻ/ ለግንባታ አማካሪ የተመደበ ሲሆን ከዚህ ዉስጥ ብር 273,300.00 / ሁለት መቶ ሰባ ሶስት ሺህ ሶስት መቶ ብር ብቻ/ 100%/ ቀደም ሲል ለተገዛው ግዥ ወጭ

ሆኖ ተከፍሏል፡፡ በመሆኑም እስከአሁን ድረስ ለዚህ ለካፒታል በጀት ከተመደበዉ ብር 10,573,000.00/አስር ሚሊዮን አምስት መቶ ሰባ ሶስት ሺህ ብር ብቻ/ ዉስጥ ብር 8,249,304.19 / ስምንት ሚሊዮን ሁለት መቶ አርባ

ዘጠኝ ሽህ ሶስት መቶ አራት ብር ከአስራ ዘጠኝ ሳንቲም ብቻ/ ተከፍሏል፡፡ በመሆኑም ብር 2,323,695.81/ሁለት ሚሊዮን ሶስት መቶ ሃያ ሶስት ሺህ ስድስት መቶ ዘጠና አምስት ብር ከሰማንያ አንድ ሳንቲም ብቻ/ ከተመደበዉ የካፒታል በጀት በችሮታ ጊዜ ስራ ላይ ይውላል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የኢንስቲትዩቱን ንብረት በተመለከተ በተለይ ብርሸለቆ ላይ ተከማችቶ ከነበረው ንብረት ውስጥ ለብአዴን 3 ዐኛ አመት ክብረ በዓል ወደ ባ/ ዳር የመጡ እቃዎች አቀማመጥን በተመለከተ ተከታታይ ጥረት ተደርጎ ለጊዜው ባህር ዳር ያሉት

ንብረቶች ፍላጎት ላላቸው የመንግስት ተቋማት እንዲተላለፉ በተሰጠው ውሳኔ መሠረት ተግባራዊ ተደርጓል፡፡

የውስጥ ገቢን በተመለከተ

የዉስጥ ገቢ ምንም እንኳ በበጀት የተደለደለ ባይሆንም የመንግስት መመሪያ በሚፈቅደዉ መሰረት በተለይ ከስልጠና ጋር ተያያዥ ለሆኑ ጉዳዮች ወጭዎችን እንዲሸፍንና በመደበኛ በጀት ዕጥረት ሳቢያ የሚሰተጓጐሉ ተግባራትን ለማከናወን እንዲውል ተደርጓል፡፡ በዚሁ መሰረት በበጀት ዓመቱ ከተደረገው ዕንቅስቃሴ፣ ባለፋት ዓመታት

ሳይከፈሉ ቀርተው የተሰባሰቡና ለስራ ወጭ የተደረገው አጠቃላይ የወጭና የገቢ ዝርዝር እንደሚከተለዉ ቀርቧል፡፡

የገቢ ዝርዝር

ከባለፈዉ አመት የዞረ ድምር ብር 22,772,019.33 ከብርሸለቆ ስልጠና የተገኘ / ተሰብሳቢ የነበረ/ ብር 20,000,000.00 ከተለያዩ ቢሮዎች ከስልጠና የተገኘና የስልጠና ቅድመ ክፍያ ብር 12,639,035.25 ከገንዘብ ቢሮ/ፒስካፕ/ በተሰባሳቢ የነበረ የስልጠና ገንዘብ ብር 1,078,510.28

7

Page 8: ReadMore

ከመዝናኛ ክበብ ገቢ ብር 164,777.67 ከጨረታ ሰነድ ሽያጭና ከዘይት ጀሪካን ሽያጭ ብር 52,485.00

ጠቅላላ የገቢ ድምር ብር 57,706,827.53

የወጭ ድምር

ለቀን እና ለኮንትራት ሰራተኛች ደመወዝ፤ እንዲሁም ለቋሚና ለኮንትራት ሰራተኛ አበል

ብር 632,980.52

ለህትመት፣ ለደንብ ልብስ፣ ለቢሮ እቃ ግዥ፣ ለምግብ፣ ለነዳጅ ብር 2,906,829.75 ለአበል፣ ለትራንስፖርት፣ ለመስተንግዶ፣ ለጥገና በወል ለሚፈፀም ግዥ ብር 636,234.34 ለስልክ፣ ለመብራት፣ ለትምህርትና ለመሳሰሉት ብር 5,244,258.08

አጠቃላይ የወጭ ድምር ብር 9,332,810.90

ተሰብሳቢ / ውዝፍ /

ከፌደራል አቅም ግንባታ ሚኒስቴር ብር 15,275,561.05 ከአብክመ ፍትህ ቢሮ ( ከክልሉ መንግስት ) ብር 1,368,050.00 ከአብክመ ገ/ኢ/ል/ቢሮ ብር 15,148,056.63 ከአብክመ ንግድ ኢንዱስትሪ ቢሮ/ በብድር የተሰጠ) ብር 421,299.30 ከአልማ ( ለህዳር 11 እስፖንሰር) ብር 69,700.00 ከብአዴን ( ለህዳር 11 እስፖንሰር ብር 52,000.00 ከአብክመ ርዕሰ መስተዳደር ፅ/ ቤት (ለህዳር 11 እስፖንሰር) ብር 54,300.00

አጠቃላይ የተሰብሳቢ ድምር ብር 32,212,966.98

ከላይ ከተዘረዘሩት ተሰብሳቢዎች በተለይ በፌደራል አቅም ግንባታ ሚኒስቴር እና በአብክመ ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ያለዉን ተሰባሳቢ በሚመለከት ለመሰብሰብ ተሞክሮ ያልተቻለ ነው፡፡

2.3 የድህረ ምረቃ ትምህርት ኘሮጀክት

የክልሉ መንግስት ከባህር ዳር ዩኒቪርስቲ ጋር በመተባበር በኢንስቲትዩቱ ውስጥ በሁለት የትምህርት ዘርፎች የድህረ ምረቃ ትምህርት እንዲጀመር አድርጓል፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ኢንስቲትዩቱ ሰፊ ተሳትፎ የነበረው ሲሆን አሁንም

ኘሮግራሙ በአግባቡ እንዲካሄድ ከዩኒቪርስቲው ጋር ተባብሮ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ ኢንስቲትዩቱ በተለይ አስተዳደራዊና ፋይናንሻል የሆኑ አገልግሎቶችን የሚሰጥ ሲሆን ለተማሪዎቹ ምቹ የትምህርት አካባቢ ለመፍጠር

እየሰራ ነው፡፡ ይህ ኘሮጀክት የክልሉ የአመራር ልማት ማዕከል /Leadership Development Centre/ ሆኖ እንዲቀጥል በኢንስቲትዩቱ በኩል ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ ከጥቅምት ወር 2003 ጀምሮ በኢንስቲትዩቱ እየተስተናገደ

8

Page 9: ReadMore

ላለው ለዚህ የድህረ ምረቃ ፕሮግራም የክልሉ መንግስት ሦስት ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ ብር የመደበ ሲሆን እስከ ሰኔ 30//2003 ያለው የወጭ ዝርዝር የሚከተለው ነው፡፡

ላፕቶፕ የተገዛበት (ለተማሪዎች) 892,645.00 ለመምህራን ወጭ

o ማስተማሪያ 444,369.98o መኝታና ምግብ 51,266.40o መጓጓዣ 17,944.00 513,580.78

የተማሪዎች የምግብ አገልግሎት 271,423.40 ለተለያዩ ስራ ማስኬጃ 32,772.95

አጠቃላይ የወጭ ድምር 1,710,421.73

በሁለቱ የድህረ ምረቃ ትምህርት ዘርፎች እስከአሁን የተሰጡ ኮርሶች

የመሸጋገሪያ ኮርሶች

Financial and managerial Accounting Organization and Human Resource Management Matimatical Economics Statistics and Econometrics Microeconomic Management Theory & Practice Marketing Management English

መደበኛ የድህረ ምረቃ ኮርሶች

Advanced Applied macroeconomics Quantitative Techniques for management Quantitative Techniques for management Information systems and knowledge management Business, Government and globalization Advanced Economics and software application Financial management and investment Analysis Advanced applied micro economic Quantitative method for Design making

9

Page 10: ReadMore

Research method for applied economics

2.4 የስልጠና ድጋፍ አገልግሎት/Facility Service/

ኢንስቲትዩቱ የሥራ አመራር ልማት ሥራዎችን ሲያከናውን ጎን ለጎን በኢንስቲትዩቱ አገልግሎት መስጫዎች ለውስጥና ለውጭ ደንበኞች ከሥልጠና ጋር የተያያዙ የስልጠና ድጋፍ አገልግሎቶችን ይሰጣል፡፡ ይህን ሥራ የሚመራው የሥራ ዘርፍ

ዕቅድ በበጀት ዓመቱ በዋናነት የተያዙትን የስልጠና ስራዎች በተገቢው ቁሳቁስ አቅርቦትና አገልግሎት አሰጣጥ ለመደገፍና ከኢንስቲትዩቱ ውጭ የሆኑ ልዩ ልዩ ተቋማትም በራሳቸው ዕቅድ የያዟቸውን ውይይቶች በኢንስቲትዩቱ

የመወያያ ክፍሎች በተሳካ ሁኔታ እንዲጠቀሙ ምቹ ሁኔታ የመፍጠር ስራ ማከናወን ነበር፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘም በበጀት ዓመቱ

ለውጭና ለውስጥ ደንበኞች የስልጠና ድጋፍ አገ/ ት ማድረግ፣ የሂደቱን የመሰረታዊ የስራ ሂደት ጥናትን ማሻሻል፣ የመወያያና የመማሪያ ክፍሎችን ለአገልግሎት ምቹ ማድረግ፣ የድምፅና የምስል ላይበራሪ ማደራጀትና አገልግሎት መስጠት፣

የእንግዳ አቀባበልና የምኝታ አገልግሎት ክፍሎችን ማደራጀት የምግብና መዝናኛ፣ የማባዣና ፎቶ ኮፒ አገልግሎትን ማመቻቸት፣ የተሟላ የመብራት፣ ውሃና የእንጨት ስራ የጥገና አገልግሎት መስጠት እንዲሁም የሚሰጡ አገልግሎቶች

የገበያ ዋጋ ጥናት ማካሄድ ትኩረት የተሰጣቸው ዕቅዶች ነበሩ፡፡

በዚሁ መሠረትም የራሳቸውን አሰልጣኝ ቀጥረው ሥልጠና በሚሰጡ ተቋማት የሥልጠና ቦታዎችንና ማቴሪያሎችን፣ የምግብ፣ የሻይና ቡና አቅርቦትና አገልግሎት በመስጠት የውስጥ ገቢ ያሰባስባል፡፡ በዚህም ኢንስቲትዩቱ የተሻለና ሁሉም

ወገኖች ሊገለገሉበት የሚችሉ የሥልጠና ማዕከል ሆኖ እንዲሰራ እየተደረገ ነው፡፡ ከዚህ አኳያ በበጀት ዓመቱ የሚከተሉት አንኳር ተግባራት ተከናውነዋል፡፡

በኢንስቲትዩቱ ውስጥ ሥልጠና ለተሰጣቸውና በራሳቸው የሥልጠና ዕቅድ ለሚሰለጥኑ 21,260 ተገልጋዮች የምግብ፣ የሻይና ቡና፣ የማሰልጠኛ ሞጁል ህትመት፣ የማስታወሻ ደብተር፣ እስኪርቢቶ አቅርቦት

ተከናውኗል፡፡ ለዚህም የብር 2,363,697 ውል ተይዟል፡፡

ለ 61 / ወንድ 58 ሴት 3/ የድህረ ምረቃ ተማሪዎች በቋሚነት የምግብና የመኝታ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ ለዚህ ተግባርም ከኢንስቲትዩቱ ብር 233,545.40 ወጭ ሆኗል፡፡

9 የማሰልጠኛና 26 የመወያያ ክፍሎችን ለተግባር ምቹ አድርጎ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡

የብአዴን 3 ዐኛ ዓመት ክብረ በዓልን አስመልክቶ ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ 6 ዐዐ ያህል እንግዶች የምግብና መኝታ አገልግሎት ከመስጠቱም ባሻገር ለ 1000 ተሰተናጋጆችም የምግብና መጠጥ አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ ተችሏል፡፡ ለተሰጠው አገልግሎትም ከተለያዩ ስፖንሰሮች ጋር በተደረገው

ውል መሠረት ሂሣቡን የማሰባሰብ ሥራ ተከናውኗል፡፡

በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ በዚህ የሥራ ዘርፍ ዕንቅስቃሴ ብር 2,363,697.00 ገቢ የሚያስገኝ ሥራ ውል ተይዞ የተከናወነ ሲሆን ለሥራው ብር 350,857.44 ወጭ ሆኗል፡፡

10

Page 11: ReadMore

2.5 የካፒታል ኘሮጀክት ሥራዎች

የኢንስቲትዩቱ ህንፃ ግንባታ ከተጀመረ ዓመታትን ያስቆጠረ ቢሆንም እስከአሁን ድረስ አልተጠናቀቀም፡፡ ኢንስቲትዩቱ ወደ አዲሱ ህንፃ በ 2 ዐዐዐ ዓ/ ም የገባ ቢሆንም መሠረታዊ የሆኑት የግንባታ ክፍሎች ያልተጠናቀቁ በመሆኑ ጊዜያዊ

ርክክብ እንኳ አልተደረገም፡፡ በህንፃዉ ላይ በተለይ ከሳኒተሪ ሥራዎች ጋር በተያያዘ በሚታዩ ጉድለቶች ሳቢያ ለሚሰጡ ሥልጠናዎች የውጭ መፀዳጃ ቤቶች በሥራ አመራር ቦርዱ ውሳኔና ፈቃድ በማሰራት ጥቅም ላይ እንዲውሉ ተደርጓል፡፡

ኢንስቲትዩቱ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት የኢንስቲትዩቱ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብባቢ፣ የክልሉ የበላይ አመራሮች፣ ኮንትራክተሩና አማካሪ ድርጅቱ በተገኙበት ህንፃው በተቻለ ፍጥነት የሚጠናቀቅበት ሁኔታ እንዲፈጠር የጋራ መድረክ

ከተፈጠረ በኋላ የተጀመሩ ስራዎችን ለማፋጠን የሚደረግ ጥረት ማሻሻል አሳይቷል፡፡ የሳኒተሪ ሥራዎች ችግርን ለመፍታትም አማካሪ ድርጅቱ ባለሙያ በመላክ ጉዳዩን ያስጠና ሲሆን ለማሻሻያ ሥራው ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ

እንደሚጠይቅ የሚያሳይ የሥራ ዝርዝር ልኳል፡፡ በዚሁ ጉዳይ ላይ የክልሉ ሥራና ከተማ ልማት ቢሮ አስተያየት እንዲሰጥበት በኢንስቲትዩቱ በኩል ተልኮ መልስ ባለመገኘቱ ባለበት ሁኔታ ማስተካከያ እንዲደረግ ታዟል፡፡

የአዳራሽ ግንባታ ሥራው እስከአሁን እንዲጠናቀቅ ቢጠበቅም አልተጠናቀቀም፡፡ የላውንደሪ ግንባታ ስራውም ገና በግንባታ ላይ ይገኛል፡፡ የዶርሚተሪን ጨምሮ የሳኒተሪ ሥራዎች ችግር ያለባቸው ቢሆኑም በአማካሪው በኩል ለማሻሻያ የቀረበው አስተያየት ከሥራና ከተማ ልማት ቢሮ ምላሽ ሊሰጠው ባለመቻሉ የማስተካከያ ስራዎች ባለበት

ሁኔታ እንዲከናወን ታዞ በመሰራት ላይ ነው፡፡ ከግንባታ አኳያ ከላይ ከተገለፀው በተጨማሪ ኢንስቲትዩቱ የሠልጣኞች ክበብ /ላውንጅ/ በጣም አስፈላጊ ሆኖ ሳለ የሌለ በመሆኑ በቀጣይ መፍትሔ ማፈላለግ የሚጠይቅ ነው፡፡

ከግቢ ውሃ እጥረት ጋር በተያያዘ ከአባይ ወንዝ የአትክልት ውሃ በመሳብ በተዘጋጀ ኘሮጀክት መሠረት የብር 1.4 ሚሊዮን ውል ተይዞ 2 ዐ% ቅድሚያ ክፍያ በመክፈል ስራው በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል፡፡ ውል ወስዶ ስራውን እየሰራው ያለውም የባ/ ዳር ከተማ ውሃ አገልግሎት ጽ/ ቤት ነው፡፡

ከፈርኒቸር አኳያ የአዳራሽ ወንበርና ተጓዳኝ ዕቃዎች ግዥ ጨረታ ወጥቶ የጨረታው ሂደት አንዳንድ ግድፈቶች የታዩበት ቢሆንም በሂደት ላይ ይገኛል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ህንጻዎች በተሟላ ሁኔታ ባለመጠናቀቃቸው ምክንያት

ከፍተኛ ገንዘብ ወጥቶባቸው የተገዙ የምግብ ቤትና የላውንደሪ ዕቃዎች ተከላ ገና አልተጀመረም፡፡

2.6 የሰው ኃይል አስተዳደርን በተመለከተ፣

የአማራ ስራ አመራር ኢንስቲትዩት መሰረታዊ የአሰራር ሂደት /BPR/ ለውጥ ጥናት በማድረግ በ 8 የስራ ሂደት / ሁለት ዋና እና 6 ደጋፊና ፈፃሚ/ በመደራጀት ተልዕኮውን በመወጣት ላይ ይገኛል፡፡

ኢ ንስቲትዩቱ በአሰራር ብቃት ያለውና ፍትሃዊ የሆነ የሰው ኃይል ልማት እና አስተዳደር ለማስፈን አቅዶ ሲሰራ የቆየ ሲሆን በበጀት ዓመቱ የኢንስቲትዩቱን የሰው ኃይል / በቅጥር፣ በደረጃ እድገት፣ በዝውውር የስልጠናና ትምህርት

ፍላጐት/ በእቅድ ለመምራት የሚያስችል እቅድ በማዘጋጀት ተግባራዊ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ በዚሁ መሰረትም የቅጥር እና ዝውውር፣ ስንብት ፣ ደረጃ ዕድገት፣ ዲሲፕሊን ጉዳዮችን በማየት በታቀደው መሰረት ተግባራት ተከናውነዋል፡፡

11

Page 12: ReadMore

በኢንስቲትዩቱ ውስጥ ከስራ ባህሪያቸው አንፃር ሶፍት፣ ሳሙና/ የገላና የልብስ/ ፣ ኤርፍሬሽነር ለሚያስፈልጋቸው የስራ መደቦች የውስጥ መመሪያ በማዘጋጀት በዚህ በጀት አመት ተግባራዊ እንዲሆን የማድረግ ስራ ተሰርቷል፡፡ ከዚህ

በተጨማሪም ከሥራው ባህሪ አኳያ በኢንስቲትዩቱ አምሽተውና ከስራ ቀናት ውጭ ገብተው ለሚሰሩ ሠራተኞች የትርፍ ስዓት ክፍያን በኢንስቲትዩቱ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ሰነድ ተዘጋጅቶ በማኔጅመንት ዉይይት

ተካሂዶበት ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል፡፡ በኢንስቲትዩቱ የደንብ ልብስ የሚያስፈልጋቸዉ እና በሲቪል ሰርቪስ የተፈቀደላቸዉ የስራ መደቦች በመለየት ሲቪል ሰርቪስ የላከዉንና የገበያ ጥናት መነሻ በማድረግ ተግባራዊ

ተደርጓል፡፡

የኢንስቲትዩቱን የሰው ኃይል በፍጥነትና በጥራት በማዘጋጀት በሰው ኃይል መመሪያው መሠረት በዝውውር፣ በዕድገትና በቅጥር የሚሟሉት ስራን በመስራት ድጋፍ የማድረግ ዕቅድ የተያዘ ሲሆን በተጨማሪም ስንብትን፣

ጥቅማጥቅምንና ዲስኘሊንን መሠረት ያደረጉ ስራዎች በሰው ኃይል አስተዳደሩ የሚሰሩ ናቸው፡፡ በበጀት ዓመቱ በኢንስቲትዩቱ ውስጥ 66 ቋሚ፣ ኮንትራት 4 ዐ ሰራተኞች (5 ሴት 35 ወንድ) 35 ተመላላሽ በድምሩ 141

ሠራተኞች ይገኛሉ፡፡

የቅጥር ፣ዕድገትና ዝውውርን በተመለከተም ከሠው ኃይል አስተዳደር አኳያ በበጀት ዓመቱ 2 ወንድ ሠራተኞች በዝውውር እንዲሁም 2 ወንድ ሠራተኞች በቋሚ ቅጥር ወደ ኢንስቲትዩቱ እንዲቀላቀሉ ተደርጓል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ

በተለያዩ ወቅቶች ለተፈጠሩ ሥራዎች 36 ሰራተኞች (32 ሴት 4 ወንድ) በጊዜያዊ ቅጥር እንዲሰሩ ተደርጓል፡፡ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ አንድ ወንድ እና አንድ ሴት ቋሚ ሠራተኞች የሥራ መልቀቂያ ተሰጥቷቸዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የኢንስቲትዩቱን ልዩ የሥራ ባህሪ ያገናዘቡ አሠራሮች እንዲቀረፁ በማድረግ ሥራ ላይ እንዲውሉ ተደርጓል፡፡ የሰው ኃይል መረጃን አደራጅቶ የመያዝ፣ የሥራ ደረጃዎች በአግባቡ ታይተው እንዲወሰኑ የማድረግና

የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ያወጣውን የድልድል መመሪያ መሠረት አድርጎ ሠራተኛ የመመደብ ተግባር ተከናውኗል፡፡ ከድልድል አኳያ በኢንስቲትዩቱ በተለያየ ስራ ሂደት የሚገኙ ሰራተኞችን ምደባ የተካሄደ ሲሆን የሠራተኛው ደረጃ

የተሻሻለበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ በዚሁ መሰረት 18 ሰራተኞች 1 ደረጃ ከፍ ብለዉ የተመደቡ ሲሆን፣ 8 ሰራተኞች 2 ደረጃ ከፍ ብለዉ፣ 14 ሰራተኞች ከ 2 ደረጃ በላይ እንዲሁም 12 ሰራተኞች ደግሞ በያዙት ደረጃ እንዲደለደሉ

ተደርጓል፡፡ በአጠቃላይ ከአስተዳደር ሰራተኞች አኳያ ከ 66 መደበኛ ሠራተኞች ውስጥ 40 ሰራተኞች ከፍ ብለዉ እንዲደለደሉ የተደረገ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ በሀገር አቀፍ የደመወዝ ማስተካከያ በኢንስቲትዩቱ ከጥር ወር

2003 ዓ. ም ጀምሮ ተግባራዊ ተደርጓል፡፡ በታሳቢነት የተመደቡ 2 ፣ ሳያሟሉ ቦታ እስኪገኝላቸው በሚል የተመደቡ እንዲሁም ተመድበውበት የነበረው መደብ በሌላ በመያዙ ምደባ ያላገኙ 1 ሠራተኞች ሆነዋል፡፡

ኢንስቲትዩቱ የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን የውስጥ ገቢ የሚያመነጭ እንደመሆኑና ሠራተኛውም ከመደበኛ ተግባሩ የበለጠ እንዲያከናውን የሚጠበቅ ከመሆኑ አኳያ ከ 1999 ዓ/ ም ጀምሮ ማበረታቻዎች እንደሚሰጡት

ይታወቃል፡፡ በተጠናቀቀው በጀትና እስከዚህ ግማሽ ዓመትም በርካታ ተግባራትን ያከናወነ ከመሆኑ አኳያ የሥራ አመራር ቦርዱ በወሰነለት መሠረት የብር 1 ዐዐሺ ማበረታቻ እንዲሰጠው ተደርጓል፡፡ ይህም ቀጣይ ተግባራትን በበለጠ ትጋት ሊፈፅም እንደሚያስችለው ይታመናል፡፡

12

Page 13: ReadMore

ትምህርትና ስልጠና በተመለከተ ኢንስቲትዩቱ

ለአንድ ወንድ የሂሳብ ኦፊሰር የኢንስቲትዩቱ ሰራተኛ በ Financial Accounting ከኢትዮ É ያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት አዲስ አበባ በመላክ/ ስልጠና እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡

ኢንስቲትዩቱ ያለውን ሠራተኛ ዕውቀትና ክህሎት ለማጐልበት ሰፊ የትምህርትና ስልጠና ተግባራትን አቅዶ አከናውኗል፡፡ በዚሁ መሠረት በበጀት ዓመቱ ከመደበኛ ትምህርት አኳያ 13 ሠራተኞችን

ለሁለተኛ ዲግሪ፣ 10 ሠራተኞችን ለመጀመሪያ ዲግሪ፣ 2 በቴክኒክና ሙያ ወጭያቸውን ሸፍኖ በማስተማር ላይ ይገኛል፡፡ ለተጠቀሰው ተግባርም በበጀት ዓመቱ ብር 1,050,665.58 ያህል

መድቦ የነበረ ሲሆን ብር 1,050,665.58 ወጭ ተደርጓል፡፡

ለአጭር ጊዜ ስልጠና አኳያም 3 ሂደት መሪዎች (1 ሴትና 2 ወንድ) በ Basic Managerial Skill ፣ 1 ሠራተኛ (ሴ) በሰው ኃይል አስተዳደር፣ 9 (7 ሴትና 2 ወንድ) በCommunicatin Skill ወደ ኢትዮጵያ ስራ አመራር ኢንስቲትዩት ተልከው ስልጠና እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡

2.7 HIV/AIDS እና ስርዓተ ጾታ በተመለከተ፣

HIV/AIDS እና ሜይንስትሪሚንግ በተመለከተ በኤች አይቪ ኤድስ ሴክሬታሪያት ጽ/ ቤት በጠየቅነው የበጀት ድጋፍ መሠረት ብር 3 ዐ ሺ ድጋፍ ማግኘቱ ቢገለጽም ኋላ በጀቱ እንደሌለ በመታወቁ የታቀዱ ተግባራት አልተከናወኑም፡፡ ሆኖም የHIV/AIDs በስራ ቦታ ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እንዲሰራ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት

እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ሲሆን ከክልሉ ኤች.ኤ.ቪ/ ኤድስ መከ/መቆ/ሴክ/ጽ/ ቤት 1008 ኮንደም በመጠየቅ በኢንስቲትዩቱ በተለያዩ ቦታዎች ለአገልግሎት እንዲዉል ተደርጓል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ከግሽ አባይ ቀበሌ ቫይረሱ

በደሙ ዉስጥ የሚገኝ አንድ ግለሰብ በኢንስቲትዩቱ የተወሰነ ድጋፍ እንዲደረግለት ተደርጓል፡፡

ስርዓተ ጾታን በተመለከተ በተለይ ሴት የኢንስቲትዩቱ ሠራተኞች የተሻለ ግንዛቤ ኖሯቸው ተግባራትን እንዲያከናውኑና ራሳቸውን ማብቃት እንዲችሉ የግማሽ ቀን ውይይት ተካሂዷል፡፡ በኢንስቲትዩቱ ሥራ አጥ ሴት ስራ ፈላጊዎችን

በመመሪያው መሠረት ቅድሚያ እንዲሰጣቸው በማድረግ እንዲቀጠሩ ተደርጓል፡፡ በኢንስቲትዩቱ ለሚዘጋጁ የሥልጠና ሞጁሎች ጾታ- ተኮር እንዲሆኑ የማድረግ ሥራ ተሰርቷል፡፡

የጾታ ድጋፍን በተመለከተ በቅጥር፣ዕድገት ዝውውርና ስልጠና ጊዜዎች ድጋፍ ተደርጓል፡፡ ዕቅዶቻችን ከስርዓተ ጾታ እኩልነት አንጻር እንዲቃኙ ድጋፍ ተደርጓል፡፡

2.8 የአገልግሎት አሰጣጥና የቅሬታ ማስተናገጃ ስራዎች

ኢንስቲትዩቱ በትኩረት ለመስራት ከያዛቸው ዕቅዶች ውስጥ የስቪል ሰርቪስ ሪፎርምን በመተግበር የአገልግሎት አሰጣጥን የማሻሻልና አገልግሎትን መሠረት በማድረግ የሚነሱ ቅሬታዎችን በተቀመጠለት የቅሬታ አቀራረብና

13

Page 14: ReadMore

አፈታት መሠረት መፍታት ይጠቀሳሉ፡፡ በእነዚህ ዕቅዶች ውስጥም የአገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርድ ማዘጋጀትና ለደንበኞች ግልጽ ማድረግ፣ አገልግሎቱን ለደንበኛ የሚመች ማድረግ፣ አስተያየት መስጫ ሳጥንና መዝገብ መጠቀም፣ የሠራተኛና የቢሮ መለያ ባጅ መጠቀም፣ የዕለት፣ የሳምንትና የወር ስራዎችን የክትትል መረጃ መያዝ ይገኙበታል፡፡ በዚሁ መነሻም የተለያዩ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡

በአገልግሎት አሰጣጣችን ዙሪያ የዳሰሳ ጥናት ተጀምሯል፡፡ በሂደቶች መካከል ውድድር እንዲፈጠር የማወዳደሪያ መስፈርቶች ተዘጋጅተው ክትትል ተደርጐባቸዋል፡፡

2.9 የህዝብ ግንኙነት ስራዎች

የኢንስቲትዩቱን ገጽታ አወንታዊ በሆነ መንገድ በመገንባት ተቋማዊና ሀገራዊ በሆኑ ጉዳዮች የጋራ መግባባት መፍጠር የሚያስችሉ ስራዎችን ለመስራት ከተያዙ ዕቅዶች ውስጥ የህትመትና የኤሌክትሮኒክስ ሚዲያዎችን

በመጠቀም የተቋሙን ዓላማና ግብ ማስተዋወቅ፣ ደንበኛ በተቋሙ የአሰራር ማንዋሎች፣ ደንቦችና ዕቅዶች ላይ ግንዛቤ እንዲኖራቸውና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማስቻል የሚሉት ይገኙበታል፡፡ በዚሁ መሰረት በያዝነው የበጀት ዓመት ውስጥ በሥራ አመራር ስልጠናዎች በተለይም በውጤት ተኮር ስርዓት፣ በመሠረታዊ የሥራ ሂደት

ለውጥ፣ በኘሮጀክት ማነጅመንት፣ በሊደርሽኘ እና በሌሎች ርዕሶች የሰጣቸው ስልጠናዎችና የምክር አገልግሎቶች እንዲሁም የስልጠና ድጋፍ አገልግሎቶችን የሚያስገነዝቡ 26 ዜናዎችን በማዘጋጀት የሚዲያ

ሽፋን እንዲሰጣቸው ተደርጓል፡፡ በክልሉ ብዙሃን መገናኛ ሬዲዮና ቴሊቪዥን፣ በአዲስ ዘመን ጋዜጣና በሌሎች ሚዲያዎች ከተሰጡ ሽፋኖች በተጨማሪም ሰሌዳዎችን በመጠቀም የኢንስቲትዩቱ ክንውኖች

በሠራተኞች ዘንድ እንዲታወቁ የማድረግ ሥራ ተከናውኗል፡፡ በኘሮግራም ደረጃ ሦስት የሬድዬ ኘሮግራም በውጤት ተኮር ስርዓት ስልጠና፣ በኢንስቲትዩቱ አገልግሎቶች እንዲሁም በተሰጡት ስልጠናዎችና የምክር

አገልግሎቶች በተቋማት ዘንድ የመጡት ለውጥና ፋይዳ ዙሪያ ተሰርቷል፡፡

የኢንስቲትዩቱን ስልጣንና ተግባር አገልግሎቶችና የውጤት ተኮር ዕቅድ እንዲሁም የማስፈፀም አቅምን የሚያስተዋውቁ ስድስት በራሪ ወረቀት ተዘጋጅቶ ለ 15 ዐዐዐ ደንበኞች ተሰራጭቷል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም

ዜና ሥራ አመራር በራሪ ጽሁፍም አራት ጊዜ ተዘጋጅቶ ለተለያዩ የመንግስት መ/ ቤቶች ተሰራጭቷል፡፡ ትኩረቱም በስልጠናዎችና በምክር አገልግሎቶች እንዲሁም ወቅታዊ ጉዳዮችን የሚያስገነዝብ ነው፡፡

ኢንስቲትዩቱ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ባከናወናቸው ስራዎችና በዕቅዱ ዙሪያ በህዝብ ግንኙነት በኩል ሁለት የኘሬስና የዜና መግለጫ፣ በኢንስቲትዩቱ ዳይሬክተር አማካኝነት ሁለት መግለጫ እንዲሁም

በተወካይ ዳይሬክተር አማካኝነት አንድ በድምር አምስት መግለጫ ተሰጥቷል፡፡ የተለያዩ መረጃዎችንና ዜናዎችን በግቢው ሰሌዳዎች ላይ በመለጠፍ መረጃዎች ለኢንስቲትዩቱ ሠራተኞች እንዲደርስ መደረጉ በምርጥ ተሞክሮነት ሌሎች ተቋማት ወስደውታል፡፡

14

Page 15: ReadMore

የብአዴንን 3 ዐኛ ዓመት የምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ የፎቶ ኤግዚብሽን ተካሂዷል፡፡ በዓሉን ለማክበር ከመጡ እንግዶች መካከልም ከ 6 ዐዐ በላይ የሆኑት ተመልክተውታል፡፡ በዓሉ በደማቅ ሁኔታ እንዲከበር በተዋቀረው ኮሚቴ አማካኝነት በተለያዩ አዝናኝና አስተማሪ ዝግጅቶች ተከብሯል፡፡

በቅርቡ ለተዘጋጁ መድረኮችም ተሳታፊዎች የሚጐበኙት የፎቶ ኤግዚብሽን ይካሄዳል፡፡ የመጽሔት ዝግጅትን በተመለከተ እንግዳችን፣ ሥራ አመራር ከየት ወደየት ሜንስትሪሚንግ፣ ውጤት ተኮር ስርዓት /BSC)፣

ደንበኞች ምን ይላሉ የሚሉትን የአምድ ፅሁፎች የያዘ በዓይነቱ ልዩ የሆነ የመጀመሪያ ሥራ አመራር መፅሄት በ 3 ዐዐዐ ቅጅ ተሰራጭቷል፡፡ ሁለተኛው መጽሄትም በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል፡፡

የህዳሴ ግድብ ግንባታን በተመለከተ የኢንስቲትዩቱ ሠራተኞች ግንዛቤ እንዲጨብጡና ለ ግድቡ ግንባታ የበኩላቸውን አስተዋጽአ እንዲያበረክቱ የውይይት መድረክ ተዘጋጅቶ በፍላጎታቸው በዓመት

የሚከፈል 1 ዐዐ% የሚከፍሉ 25 ሠራተኞች እንዲሁም 5 ዐ% የሚከፍሉ 77 ሠራተኞች ውሳኔያቸውን አስታውቀዋል፡፡ በዚህም መሠረት ከ 91,683.43 / ዘጠና አንድ ሺህ ስድስት

መቶ ሰማኒያ ሦስት ብር ከአርባ ሦስት ሣንቲም/ ከግንቦት ወር ጀምሮ ገቢ ማድረግ ተጀምሯል፡፡ ከቦንድ ግዥ አኳያ ኢንስቲትዩቱ የ 1 ሚሊዮን ብር ቦንድ የገዛ ሲሆን የኢንስቲትዩቱ ሠራተኞችም

በተደረገው የጋራ ውይይት በግል የብር 25000.00 / ሃያ አምስት ሽህ ብር/ ቦንድ ገዝተዋል፡፡ ይህን ድጋፍ

የሚያጠናክር አስተባባሪ ኮሚቴም በኢንስቲትዩቱ ውስጥ የተቋቋመ ሲሆን ሠራተኞችን በማስተባበር በቦንድ ግዥ እንዲሳተፉ የተለያዩ ጥረቶችን እያደረገ ይገኛል፡፡ በቅርቡም

በክረምት የሚሰሩ ስራዎችን አስመልክቶ የሞባላይዜሽን ዕቅድ አዘጋጅቷል፡፡

መድረክ ማመቻቸትን አስመልክቶ የዕቅድ አፈጻጸም መድረክ ከሠራተኛው ጋር ሶስት ጊዜ፣ ሁለት መድረኮች ከደንበኞችና ባለድርሻ አካላት ጋር በዋና ተልዕኮአችንና በግዥ ስርዓታችን ዙሪያ እንዲፈጠር ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል፡፡

3. በእቅድ አፈጻጸም ወቅት ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ የመፍትሄ እርምጃዎች

- በአዲስ እና በማሻሻል የተዘጋጁ የስልጠና ሞጁዉሎች ላይ በተሰጠው አሰተያየት መሰረት ግብአቱን ተጠቅሞ በወቅቱ አስተካክሎ ያለማጠናቀቅ/ ያለማስረከብ፤

- አልፎ አልፎ የሚሰጥ የስልጠና ስምሪትን ላለመቀበል የሚደረግ ክርክር፤

15

Page 16: ReadMore

- አንዳንድ ተቋማት በተለይም በአማራ የዘላቂ ውሀ ማሰባሰብ ፕሮጀክት (SWHISA) ከኢንስቲትዩቱ ጋር በገባው ውል መሰረት ተካሄደውን የስልጠና ክፍተት ጥናት መሰረት አድርጎ በተዘጋጀው የስልጠና ፕሮግራም መሰረት ( ከየካቲት

5-22/2003 ዓ/ም) ስልጠና አለመሰጠቱ ሌሎች ስልጠናዎች የሚሰጥበትን ጊዜና የሰው ሀይል ማባከን፤

- ሠልጣኝ የሚልኩ ተቋማት አስቀድመው የሰልጣኝ ፕሮፋይል (አሟልተው) ያለመላክ፤ እንዲሁም በፕሮግራም ካስያዙት የሰልጣኝ ቁጥር በላይ መላክ( የውሀና ፍሳሽ አገልግሎት)፤

- አንዳንድ ተጋባዥ አሰልጣኞች እንዲያሰለጥኑ በሚያዝላቸው ፕሮግራም አወንታዊ ምላሽ ያለመስጠት /ለማሰልጠን ፈቃደኛ ያለመሆን፤

- ተቋማት ከኢንስቲትዩቱ ውጪ የድጋፍ አገልግሎት እንዲሰጣቸው ሲጠይቁ አማካሪዎች አሁን በስራ ላይ ያለው የውሎ አበል መጠን አያሰራም የሚል ቅሬታ ማቅረብ፤

- ለሂደቱ የሚያስፈልጉ እቃዎች በወቅቱ ያለመገዛት የቋሚ ዕቃ ኮድ መስጫ መሳሪያ በገበያ ላይ አለመገኘቱና ኮድ መሰጠት አለመቻሉ፣

- ግዥ ፈላጊዎች ስፔስፊኬሽን ለይቶ ያለማቅረብ፣

- የመደበኛ በጀት ሲመደብ አነስተኛ መሆን፣

የተሰጡ መፍትሄዎች

- በተዘጋጀው የሁለተኛ ግማሽ አመት ውጤት ተኮር እቅድ ላይ ፈጻሚው በእቅድ እንዲይዘው ተለይቶ ተሰጥቷል፤

- የሂደት አማካሪዎች አቅም ማሳደጊያ ስልጠናዎችን ከሚመለከተው አካል ጋር በመሆን ማማቻቸትና ስልጠናው እንዲሰጥ መከታተል፤

አማካሪዎቹ በሰለጠኑት መሰረት ስልጠናና ምክር አገልግሎቶች በተቀናጀ እና ተከታታይ በሆነ መንገድ እንዲሰሩ ማመቻቸት፤ የኮድ መስጫ መሳርያ እስኪገኝ ድረስ በቀለም/በፓርከር/ኮድ መስጠት፣

ስፔስፊኬሽን ለይተዉ እንዲያቀርቡ ተደርጓል ፣

የውስጥ ገቢ በጀትን መጠቀም ችግሩን ለማቃለል ጥረት ተደርጓል፡፡

16

Page 17: ReadMore

የ 4 ኛ ሩብ አመት ዕቅድ አፈፃፀም

ተ/ቁ

የታቀደው ተግባር ዝርዝርዕቅድ አፈፃፀም አፈፃፀ

ምመግለጫ

በበጀት አመት

የዚህ ሩብ አመት

እስከዚህ ሩብ አመት

የዚህ ሩብ አመት አፈፃፀም በ%

እስከዚህ ሩብ አመት

ወ ሴ ድ ወ ሴ ድ

1. የስልጠና አገ / መስጠት ውጤት ተኮር ስርዓት (BSC) 810 - 810 406 117 52

31035

259 1294

159% በዘመቻ ለ 1460 ሰዎች የተሰጠው

ስልጠናን አይጨምርም

Team building & coaching 1134 384 1134 34 7 41 10.67%

34 7 41 3.6%

ለመንግስት ሰራተኞች ፖሊስዎችና ስትራቴጀዎችን ማስተዋወቅ 1000 400 1000

- - - - በሲቪል ሰርቪስ ቢሮ የተያዘ ስለነበር

አልተፈፀመም

TQM ስልጠና መስጠት 100 - -- - - - - ኘሮጀክት ስራ አመራር 500 200 500 38 8 46 116 13 129 25.8

% በቢሮ አስተዳደርን ሪከርድ ስራ አመራር 248 90 248 3 88 91 101% 4 126 130 52.4

% የፋይንናስ ስራ አመራር 100 50 -- - - - - - - - በደንበኛች አገልሎት አሰጣጥ 500 200 500 - - - - 27 23 50 10%

የለውጥ ስራ አመራር 302 100 302 36 7 43 43% 36 7 43 14.23%

Entrepreneurship / ሥራ ፈጠራ/ 150 -- 150 - - - የሰው ኃይል ስራ አመራር 302 -- 302 - - -

Transformational leadership 302 -- 302 33 8 41 - 61 10 71 23.5%

ድምር 61.6%

17

Page 18: ReadMore

ተ/ቁ

የታቀደው ተግባር ዝርዝርዕቅድ አፈፃፀም

አፈፃፀም

መግለጫበበጀት አመት

የዚህ ሩብ አመት

እስከዚህ ሩብ አመት

የዚህ ሩብ አመት አፈፃፀም በ%

እስከዚህ ሩብ አመት

ወ ሴ ድ ወ ሴ ድ2 የስልጠና ሞጅውል ዝግጅት

የስልጠና ሞጅል ማሻሻል 2 6 በአዲስ ማዘጋጀት የንግድ ሥራ ሞጅል 1 1

የተሻሻል በአዲስ የተዘጋጀ የስልጠና ሞጅሎችመገምገም

3 3

3 ምክር አገ / መስጠት ቢሮዎች 14 - 14 - - - 14 100 የልማት ድርጀቶች 2 - 4 - - - 4 200

4 ጥናትና ምርምር ስራ የBPR ስኬት 1 1

የከተማ አስተዳደር አገ/ አሰጣጥ 1 1 1 100%

5 የሂደቱ አማካሪዎችን የ ስልጠና አቅም ማሳደግcoaching & mentoringResearch &module development consulting methods 19 19 - 23 የሂደቱ አማካሪዎች

ስቪል ሰርቪስ ቢሮ ከየሂደቶች

TQM 19 19 -- 19advanced computer 18 18 -- --transformational leadership 19 19 -- --TOT 10 10 - 22 የሂደት አማካሪና የኦዲት

ቢሮ ስቪል ሰርቪስ ቢሮ የክትትልና ግምገማ ዘዴ (M&E) 2 2 -- --

18

Page 19: ReadMore

6 ልምድ ልውውጥ የከፍተኛ ትም/ ተቋማትን

--

የኢት/ ስራ አመራር ኢንስቲትዩት7 መረጃን መያዝ

- የስልጣኞች በየዙሩ- የተዘጋጅ የስልጠና ሞጅሎችን- የአማካሪዎች- የየወቅቱ ሪፖርቶች

4 4 2 2 4 4 100%የተከናወነ

19

Page 20: ReadMore

በክልሉ መንግስት የተመደበ በጀት መግለጫ

ተ.ቁ ዋና ዋና ተግባራት የአመቱ በጀት ዕቅድ

የበጀት አመቱ ክንዉን ምርመራ

1 መደበኛ በጀት ብር ብር

1.1 ደመወዝ 1,100,000.00 1,384,636.76 የደመወዝ ጭማሪ በመደረጉ

1.2 የወንበር አበል 8,800.00 8,7 87.00

1.3 6% ጡረታ 66,000.00 83,023.00 የደመወዝ ጭማሪ በመደረጉ

1.4 ስራ ማስኬጃ 1,344,207.00 1,343,533.65

2 ካፒታል በጀት

2.1 ለግንባታ አማካሪ 273,300.00 273,300.00

2.2 ለፈርኒቸር ግዥ አማካሪ 299,700.00 53,539.79 በፊት ለተገዛዉ ግዥ

2.3 ለፈርኒቸር ግዥ 3,000,000.00 0.00 ግዥ ባለመፈፀሙ

2.4 መኖርያ ላልሆኑ ህንፃ ግንባታ 7,000,000.00 7,922,464.40 ከፈርኒቸር ግዥ በመጠቀም /በማዛወር/

20